Posts

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የቡና ኮንፈረንስ እንድታዘጋጅ ተመረጠች

- ውድድሩ አፍሪካና አውሮፓን አፎካክሯል በዓለም አቀፍ የቡና ግብይት ውስጥ ከፍተኛውን ሚና የሚጫወቱት ቡና ገዥ ኩባንያዎችና አምራቾች በአባልነት የታቀፉበት ዓለም አቀፍ የቡና ድርጅት፣ ኢትዮጵያ አራተኛውን ዓለም አቀፍ የቡና ኮንፈረንስ እንድታዘጋጅ መረጠ፡፡ እ.ኤ.አ. በማርች 2016 የሚዘጋጀውን ኮንፈረንስ ለማስተናገድ የመጨረሻው ውድድር ላይ ቀርበው የነበሩት ኢትዮጵያና ጣሊያን ናቸው፡፡ ምርጫው በተካሄደበት  ለንደን ከተማ ተገኝተው የነበሩ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን አባላት እንደገለጹት፣ ውድድሩ ከፍተኛ ፉክክር የነበረበት ቢሆንም ኢትዮጵያ ልታሸንፍ ችላለች፡፡  በመጨረሻው ውድድር ላይ ከድምፅ ሰጪዎች መካከል ግዙፎቹ የአውሮፓ ቡና ገዥ ኩባንያዎች ድምፃቸውን ለጣሊያን ሰጥተው ነበር፡፡ አፍሪካውያንና ሌሎች ቡና አብቃዮች ደግሞ ለኢትዮጵያ ድምፅ በመስጠት ውድድሩ በአፍሪካውያንና በአውሮፓውያን መካከል እንዲሆን አድርገው ነበር ብለዋል፡፡ በተለይ በዓለም አቀፉ ድርጅት ውስጥ ከፍተኛ ድምፅ ካላቸው አገሮች መካከል አንዷ የሆነችው ብራዚል ድምጿን ለኢትዮጵያ በመስጠቷ ለኢትዮጵያ አሸናፊነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል ተብሏል፡፡ ከመጨረሻው ውድድር ቀደም ብሎ ኮንፈረንሱን ለማዘጋጀት ከአፍሪካ ኮትዲቯር፣ ጋቦንና ኬንያ ጥያቄ አቅርበው የነበረ ቢሆንም ሁሉም አገሮች የኢትዮጵያን የተወዳዳሪነት ጥያቄ በመቀበል ድምፃቸውን ሰጥተዋታል፡፡ ኮንፈረንሱ አፍሪካ ውስጥ መካሄዱ ትልቅ ዕድል ነው በማለት ለኢትዮጵያ ዕድሉ እንዲሰጣት አፍሪካውያኑ ድጋፍ እንዳሰባሰቡም በቦታው ከነበሩ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን አባላት ለመረዳት ተችሏል፡፡  ከዓለም የቡና ድርጅት (አይሲኦ) መካከል 50 በመቶዎቹ የቡና ገዥ ኩባንያዎች የሚወከሉባቸው አገሮች ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ ቡና አምራች አገሮች

ዋና ኦዲተር ለብክነት የተጋለጡ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ሒሳቦችን አጋለጠ

Image
- ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ያልተሰበሰበ ሒሳብ አለ -785 ሚሊዮን ብር ሕጋዊ ያልሆነ ወጪ ታይቷል -ከ2.3 ቢሊዮን ብር በላይ ያልተሠራበት በጀት ተገኝቷል የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ላለፉት በርካታ ዓመታት ለፓርላማ ሲያቀርበው እንደቆየው ሁሉ፣ ለብክነት የተጋለጠ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የመንግሥት ሀብት መኖሩን ባለፈው ሚያዝያ 14 ቀን 2006 ዓ.ም. ለፓርላማው ይፋ አድርጓል፡፡ ተመሳሳይ ሪፖርቶችን ሲሰማ የቆየው ፓርላማው ፈጣን ዕርምጃ ከመውሰድ ይልቅ የአንድ ዓመት ገደብን መስጠት መርጧል፡፡ በዝቅተኛ የደመወዝ ክፍያ ምክንያት ሠራተኞችን ለማቆየት መቸገራቸውን የገለጹት የፌደራሉ ዋና ኦዲተር አቶ ገመቹ ዱቢሶ፣ ችግሩን ለመቅረፍ ራሳቸው ጭምር በቡድን መሪነት በተሳተፉበት የ130 የፌደራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶችን የ2005 ዓ.ም. በጀት ኦዲት በማድረግ፣ እንዲሁም በኦዲት ሰርቪስ ኮርፖሬሽን የስምንት መሥሪያ ቤቶችን ኦዲት በማሠራት፣ በአጠቃላይ የ138 መሥሪያ ቤቶችን ኦዲት በመተንተን የኦዲት ግኝቱን ለፓርላማ አቅርበዋል፡፡ ከቀረበው የፋይናንስ ሕጋዊነትን የተመለከተ የኦዲት ሪፖርት ውስጥ አንድ ቢሊዮን 527 ሚሊዮን ብር ተሰብሳቢ ሒሳብ መኖሩን፣ ሕጋዊ ሥርዓቱን በልተከተለ መንገድ የተለያዩ የመንግሥት ድርጅቶች 785 ሚሊዮን ብር ወጪ ማድረጋቸውን፣ የተፈቀደው በጀት በትክክል ሥራ ላይ መዋሉን ለማረጋገጥ በተደረገ ኦዲት ደግሞ 2.3 ቢሊዮን ብር ያልተሠራበት በጀት መገኘቱን ይፋ አድርገዋል፡፡ ውዝፍ ተሰብሳቢ ሒሳብ ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት በወቅቱ ካልተወራረደ ወይም ካልተሰበሰበ በቆየ ቁጥር የመሰብሰብና ወደ ሀብትነት የመለወጥ ዕድሉ አሳሳቢ መሆኑን የገለጹት ዋና ኦዲተሩ፣ ኦዲት ከተደረጉት መሥሪያ ቤቶች 77 በሚሆኑት ላይ 877.1

ታስረው የከረሙት የሲዳማ ተማሪዎች በነጻ ተለቀቁ

በሃዋሳ ከተማ በኣላሙራ እና በታቦር ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የምማሩ የሲዳማ ተማሪዎች በየትምህርት ቤቶቹ ለሲዳምኛ ቋንቋ ትኩረት ተነፍጎታል በማለት ሲዳምኛ ቋንቋ በትምህርት ቤቶቹ የሰራ ቋንቋ መሆን ኣለበት በምል እና ሌሎች የመብት ጥያቄዎችን ኣክለው ድምጻቸውን ባሰሙ ተማሪዎች እና በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች በማካከል በተፈጠረው ግጭት የታሰሩት ተማሪዎች በኣሽባርነት ለመክሰስ መንግስት እየተዘጋጀ ነው ብባልም ከደረሰበት ከፍተኛ የህዝብ የተቃውሞ ግፍት ተማሪዎችን ተመክረው መለቀቃቸው ታውቋል።

የአዲስ አበባና የኦሮምያ ልዩ ዞን የጋራ ማስተር ፕላን እያወዛገበ ነው፤ የሃዋሳውስ?

Image
ሰሞኑን የኣዲስ ኣበባና ኦሮሚያ ልዩ ዞን የጋራ ማስተር ፕላን እያወዛገበ መሆኑን ተሰምቷን። የጋራ ማስተር ፕላኑ በኦሮሚያ የፖለትካ ተቃዋሚዎች ብቻ ሳይሆን በክልሉ ገዥ ፓርቲ ኣባላት ጭምር ድጋፍ ተነግፎታል። ለመሆኑ የሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር እና ሲዳማ ዞን ምን ኣስበው ይሁን ? ዞሮ ዞሮ እነርሱም ወደ ጋራ ማስተር ፕላን መግባታቸው ኣይቀርምእና። ለማንኛውም የኣዲስኣበባው እና ኦሮሚያ ልዩ ዞን ወዝግብ ከታች ያንቡ፦ ተቃዋሚዎች የጋራ ፕላኑን ተቃወሙ ዕቅዱ የአዲስ አበባን የመሬት ችግር ለመፍታት እንጂ ለልማት አይደለም - (ኦፌኮ)      አዲስ አበባንና የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞችን በልማት ለማስተሳሰር ላለፉት ሁለት ዓመታት ጥናት ሲካሄድ የቆየ ሲሆን፤ የተቀናጀ የጋራ ልማቱን ለመተግበር የተዘጋጀው የጋራ ማስተር ፕላን ባለፈው ሳምንት በአዳማ በተካሄደ የአሰልጣኞች ስልጠና ላይ ለውይይት ቀርቦ ነበር፡፡  የአዲስ አበባንና የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞችን የ10 ዓመትና 25 ዓመት የልማት ዕቅዶች የያዘው የጋራ ማስተር ፕላን የተለያዩ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና አስተዳደራዊ ጥያቄዎችና ስጋቶችን የቀሰቀሰ ሲሆን ህገ መንግስታዊ ጥያቄም አስነስቷል፡፡  የኦሮሚያ ልዩ ዞን እስካሁን የአዲስ አበባ  ቆሻሻ መጣያ ሆኖ እንደቆየ የጠቀሱት አንድ የውይይቱ ተሳታፊ፤ አንድ ከተማ ዕቅድና ፕላን ይዞ ሲነሳ የራሱ ፖሊሲ አይኖረውም ወይ?” ሲሉ ጠይቀው “አንዱ ተቀባይ አንዱ ሰጪ ሆኖ እስከመቼ ይዘለቃል? ብለዋል፡፡ ልዩ ዞኑ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ እንደመኖሩ ጨፌ ኦሮሚያ በዞኑ ላይ የመወሰን ስልጣን አለው የገለፁት እኚሁ ተናጋሪ፤ ጨፌ ኦሮምያ በጉዳዩ ላይ ሳይወያይና ሳይወስን ወደ ተግባር ከተገባ ስልጣን መጋፋት አይሆንም ወይ?” በማለት አስረግጠው ጠይቀዋል፡፡ ሌላው አስተያየት ሠጪ በበ

Invitation to the 12th Commemorative Anniversary of the Sidama Looqqe Massacre – May 24, 2014 in London, England

Image
The following is a message from the Sidama Community in the UK. The Sidama community UK is planning to hold the 12th Commemorative Anniversary of Sidama’s Looqqe massacre of May 24, 2002. The event will take place in London on May 24, 2014 starting at 1pm – to wrap up at 9pm. In addition to the above, during this conference, there will be series of programmes due to take place in conjunction with the commemoration. This will be the recently established campaign group known as the ‘Human Rights Advocacy Group,’ (HRAG), whose founding members include the Oromo, Sidama, Ogaden Somali, Gambela, Benshangul and Shakacho. HRAG presents its report and discusses the way forward. HRAG was inspired by us during last years’ Sidama Looqqe massacre 11th Commemoration program in London. Challenges faced and opportunities available to advance our noble causes will be discussed; resolutions will be sought. There will be also critical discussion on current affairs involving the uprooting of O