የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ፤ በሲዳማ ቡና ገበያ ላይ ተጽኖ ይኖረው ይሁን?
ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት ለመዘርጋት ምሳሌ ይሆናል የተባለውን የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የቆዩትን ዶ/ር እሌኒ ገብረ መድኅንን ተክተው ሲሠሩ የቆዩት አቶ አንተነህ አሰፋ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ፡፡ ምንጮች እንደጠቆሙት አቶ አንተነህ ከኃላፊነት የለቀቁት አሜሪካ ሆነው ባመለከቱት የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ ሲሆን፣ የምርት ገበያው ቦርድ ጥያቄያቸውን ተቀብሎ አፅድቆታል፡፡ በቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ አዲሱ ለገሰ ሊቀመንበርነት የሚመራው የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ቦርድ የሥራ መልቀቂያውን ተቀብሎ ውሳኔ የሰጠው፣ ሐሙስ መጋቢት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. መሆኑን የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡ አቶ አንተነህ ሥራቸውን ለመልቀቅ ውሳኔ ላይ ያደረሳቸው የጤና ችግር መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በልብ ሕመም ምክንያት በአገር ውስጥ በሕክምና ላይ እንደነበሩና አነስተኛ ቀዶ ጥገና ተደርጐላቸው እንደነበር ታውቋል፡፡ በዚህ ምክንያት ለከፍተኛ ሕክምና አሜሪካ የሄዱት አቶ አንተነህ፣ ሕክምናውን እዚያው በቅርብ እንዲከታተሉ በመወሰኑ ሥራቸውን ለመልቀቅ እንደተገደዱ እየተነገረ ነው፡፡ ወደ አሜሪካም ሲጓዙ ቤተሰቦቻቸውን ይዘው እንደሆነም ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡ በሥራ ገበታቸው ላይ ሳይገኙ ከሁለት ወራት በላይ የቆዩት አቶ አንተነህ፣ ይመለሳሉ ተብሎ በሚጠበቅበት ጊዜ የሥራ መልቀቂያ መላካቸው ያልተጠበቀ ነው ተብሏል፡፡ አቶ አንተነህ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሙሉ የምርት ገበያውን ኃላፊነት ተረክበው መምራት ከመጀመራቸው ቀደም ብሎ፣ ከነሐሴ 24 ቀን 2004 ዓ.ም. እስከ መስከረም 20 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ ዕጩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተብለው ከዶ/ር እሌኒ ጋር በጋራ ሲሠሩ እንደነበር ይታወሳል፡፡ መስከረም