Posts

የሙሲና ነገር በኢትዮጵያ!

Image
Petty Corruption Rife in Ethiopia Although the latest survey suggested that petty corruption is common, grand corruption is not an issue Ameha Diana, director general of Selam Development Consultants Plc, left, and Wedo Atto, the deputy Commissioner of FEACC during the presentation on Thursday, January 23, 2014. The first draft of the World Bank sponsored corruption study comes out pointing fingers at petty corruption in various government institutions, while playing down the impact of grand corruption. The power, tax, investment and transport sectors have been identified as having the highest level of corruption, according to a draft finding by a study under the Federal Ethics & Anti-Corruption Commission (FEACC). Employees of the Ethiopian Electric Power Corporation (EEPCo) have been identified by the study as being frontrunners in asking for unofficial payments, with an average of 10 bribe requests for a single respondent in the study. The EEPCo is als

“የግንቦት 20 ፍሬን የምንለካው ኢህአዴግ በሰላማዊ መንገድ ከሥልጣን ሲወርድ ነው”

Image
ጭቆና ትግልን ያጠነክራል እንጂ አይገድልም... ኢህአዴግን በምርጫ ለማሸነፍ የአንድ ወር ሥራ በቂ ነው…. ኢህአዴግ ሁልጊዜ የትግራይ ህዝብ በስጋት እንዲኖር ነው የሚፈልገው  በቅርቡ ለፓርቲዎች የውህደት ጥያቄ አቅርባችኋል፡፡ ለየትኞቹ ፓርቲዎች ነው ጥያቄውን ያቀረባችሁት? መስፈርታችሁስ ምን ነበር? እኛ እንግዲህ ያሰብነው በመድረክ ውስጥ ካሉት ፓርቲዎች ጋር ውህደት ለመፈፀም ነው፡፡ ግን ከመድረክ ውጪም ቢመጣ ችግር የለብንም፡፡ እንግዲህ በጠየቅናቸው ፓርቲዎች ሙሉ ፈቃደኝነት በቅርቡ ከግንባር ወደ ውህደት እንሄዳለን የሚል እምነት ነው ያለኝ። ጥያቄውን ለኦፌኮ፣ ለአንድነት እና ለደቡብ ህብረቶች አቅርበናል፡፡ እነሱም በጐ ምላሽ እየሰጡን ነው፡፡ ውህደት የተጠየቁት ፓርቲዎች የመድረክ አባል ከሆኑ ለምን ራሱን መድረክን አልጠየቃችሁም? ፓርቲዎቹን በተናጠል መጠየቅ ለምን አስፈለገ? ሁለት አቅጣጫ ነው ያለው፡፡ እንዳልከው በቀጥታ መድረክንም መጠየቅ ይቻል ነበር፤ ግን በተናጠል የመጠየቁን መንገድ ነው የመረጥነው፡፡ ይሄን ጥያቄ ያነሳሁት “አረና በመድረክ ላይ እምነት የለውም” የሚሉ አስተያየቶች ስለሚሰነዘሩ ነው… በተናጠል መጠየቁን በመድረክ ህልውና ካለማመን የመጣ ነው የሚሉ ወገኖችም አሉ… እኛ እኮ ሁሉንም ነው የጠየቅነው፡፡ ነጥለን የተውነው ፓርቲ ቢኖር ሊያስብል ይችላል፡፡ ግን የጠየቅናቸው በአጠቃላይ በመድረክ ውስጥ ያሉትን ነው:- አረና፣ ኦፌኮ፣ አንድነት እና የደቡብ ህብረት፡፡ አረና ተነሳሽነቱን ወስዶ ነው የእንዋሃድ ጥያቄውን ያቀረበው፡፡ ስለዚህ መድረኩን አይፈልጉትም የሚያስብል ሁኔታ አይፈጥርም፡፡ ይሄኛውን መንገድ መምረጣችን ብዙም ችግር አለው ብዬ አላስብም፡፡ ለውህደቱ ጥያቄ መነሻችሁ ምንድን ነው? እንዴትስ ይሄኛውን ጊዜ መረጣችሁ? ምናልባት ምርጫው

ሂውማን ራይትስ ዎች በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩ ይበልጥ ጠቧል አለ

Image
መንግስት፤ ተቋሙ የተቃዋሚዎች የፕሮፖጋንዳ ማስፈፀሚያ ነው “በኢትዮጵያ የነፃ ሚዲያ ህልውና አደጋ ላይ ነው” “በኤርትራ የመብት ጥያቄ ማንሳት ነውር ሆኗል” ብሏል የኢትዮጵያ መንግስት የዜጐችን  ሰብአዊ መብት በስፋት ይጥሳል በማለት ተደጋጋሚ ወቀሳና ስሞታ የሚያቀርበው ሂውማን ራይትስ ዎች የተሰኘው አለማቀፍ የመብት ተቋም፤  ሰሞኑን ይፋ ባደረገው አመታዊ ሪፖርቱ፣ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ነፃነት ይበልጥ መጥበቡንና የነጻ ሚዲያ ህልውና አደጋ ላይ መውደቁን ገለፀ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ፤ የተቋሙን ሪፖርት ያጣጥላል፡፡ በአገሪቱ ውስጥ የፖለቲካ ነፃነትና የፖለቲካ እንቅስቃሴ የማካሄድ እድል (የፖለቲካ ምህዳር) እየጠበበ የመጣው ከምርጫ 97 በኋላ መሆኑን የገለፀው ሂውማን ራይትስ ዎች፤ ከዚያ ወዲህ በመንግስት የፀደቁትን የፀረ - ሽብር እና የበጐ አድራጐት ማህበራት አዋጆችን በምሳሌነት ጠቅሷል፡፡ በፀረ - ሽብር አዋጁ መነሻነት ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች ሽብርተኛ ተብለው እንደታሠሩና እንደተፈረደባቸው የተቋሙ ሪፖርት ጠቅሶ፣ በህጋዊና ሰላማዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፍርሃት እንዲሸበቡ ተደርገዋል ብሏል፡፡  ጋዜጠኞች የፀረ-ሽብር አዋጁን በመፍራት የሙያ ተግባራቸውን እንዳያከናውኑ መታፈናቸውን ሲገልጽም፤ የአዋጁ አንቀፅ እየተጠቀሰ እሥራት የተፈረደባቸው ጋዜጠኞች መኖራቸውንም አውስቷል፡፡ በኢትዮጵያ ጐልተው የሚታዩት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች የፖለቲካ ምህዳር መጥበብና የኘሬሶች አፈና ቢሆኑም፤ ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችም መሻሻል አላሣዩም ብሏል ሪፖርቱ፡፡  በማረሚያ ቤት ያሉ እሥረኞች በገለልተኛ አካላት እንዳይጐበኙ መከልከል፣ ያልተፈረደባቸው ግለሰቦችን አስሮ ማቆየትና ለፍርድ ቤት አቤቱታ እንዳይቀርቡ ማገድ፤ ያልተፈረደባቸውን ሰዎች በብሔራዊ ቴሌቪዥን

ሲዳማ እና የጫት ምርቷ

Image
በሪፖርተራችን በጥቻ ወራና የቀረበ የሲዳማ ጫት ገበያ እንደተለመደው ዘንድሮም ሞቅ ያለ ነው። እንደምታወቀው በተለይ በበጋ ወራት የጫት ገበያው ሞቅታ ከፍተኛ ይሆናል ምክንያቱ በበጋ ወራት የጫት ምርት ኣነስተኛ ስለምሆን ነው። በተቃራኒው በክረምት የጫት ምርት ከፍተኛ ስለምሆን እና ኣብዛኛዎቹ የጫት ኣምራቾች ምርታቸውን በገፍ ይዘው ወደ ገበያ ስለሚወጡ የጫት ዋጋ ይቀንሳል። የሲዳማ ጫት ምርት በመላው ኣገሪቷ ተፋላጊነቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ የተነሳ የሲዳማ ኣርሶ ኣደሮች ሌሎች ለምግብነት የምሆኑ የእርሻ ምርቶችን ማምረት ትተው ማሳቸውን በጫት በመሸፈን ላይ ናቸው። በኣሁኑ ጊዜ በሲዳማ ውስጥ 60 ከመቶ የምሆነው መሬት በጫት በመያዝ ላይ ነው ብባል ውሽት ኣይደለም፤ ምክንያቱም ኣነሰም በዛም በ 21 ዱም የሲዳማ ወረዳዎች ውስጥ ጫት ይመረታልና። በጣም የምገርመው ከዚህ በፊት በቡና ምርቱ ይታወቅ የነበረው የኣለታ ጩኮ ወረዳ በኣሁኑ ጊዜ በኣብዛኛው የእርሻ መሬት የጫት የተያዘ ነው። በሲዳማ ውስጥ ባሉት ከዚህ በፊት ጫት በማይመረትባቸው ኣሮሬሳን የመሳሰሉ ወረዳዎችን ጨምሮ በሁሉም ወረዳዎች ጫት በመረቱ ከጫት የምገኘው ገቢ ከሌላው የእርሻ ምርት ከምገኘው ገቢ በላይ በመሆኑ በመሆኑን መገመት ኣያስቸግርም። ለዚህም ይመሰላል ሲዳማ ውስጥ የቡና ተክል እየቆረጡ ጫት እየተከሉ ያሉ ኣርሳ ኣደሮች ቁጥር እየተበራከተ መምጣቱ። ሲዳማ ለምግብነት የሚሆን ምርት ማምረት ኣለበት ወይስ ካሽ ክሮፕ ወይም የተሻለ ገቢ የሚያስገኙ እንደጫት ኣይነት ምርቶችን ማምረት ኣለበት በምለው ዙሪያ ብዙ ኣከራካሪ ጉዳዮች ልኖሩ ይችላሉ፤ ከዚህም ባሻገር ሰው በገዛ ማሳው የሚያዋጣውን ምርት የማምረት መብት ሰላሌው ክርክር ውስጥ ኣንገባም። ሲዳማ

የሃዋሳ ኤርፖርት የግንባታ ቦታ ለውጥ እና መዘዙ

Image
የኤርፖርቱ ግንባታ ቦታ ለውጡን ተከትሎ የሞሮቾ ሾንዶላና ቀበሌ እና የኣከባቢው ቀበሌያት ነዋሪዎች ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውስ ውስጥ ገብተዋል። የሃዋሳ ከተማ በተለይ ካለፉት ጥቂት ኣመታት ወዲህ ከፍተኛ ሁለ ገብ እድገት በማስመዝገብ የነዋሪዎቿን ብቻ ሳይሆን የኣገር ውስጥ እና የውጭ ኣገር ዜጎችን መሳብ መጀመሯ የምታወቅ ነው። ከተማይቱ ከኣዲስ ኣበባ በቅርብ ርቀት ላይ መገኘቷ እና ምቹ የምድር ትራንስፖርት ፍሰት ያላት መሆኑ ኤርፖርት ሳይኖራት እንድትቆይ ምክንያት ሆኗል። የሆነ ሆኖ ሰሞኑን የመንግስት ዜና ኣውታሮች ለዘመናት ያለ ኤርፖርት የቆየችው ይችው የሲዳማ መዲና ሃዋሳ፤ የኤርፖርት ባለበት እንድትሆን ኤርፖርት ልገነባላት መሆኑን ማብሰራቸውን ተከትሎ በርካታ የሃዋሳ ነዋርዎች እንድሁም ኣጠቃላይ ሲዳማውያን ደስታቸው በተለያየ መንገድ ስገልጹ ከርመዋል። በኣሁኑ ጊዜ በሲዳማ የኤርፖርቱ ግንባታ ቁጥር ኣንድ የመወያያ ኣርዕስት ሲሆን፤ በተለይ የቦታ መረጣው የብዙዎቹን ቀልብ የሳበ ጉዳይ ሆኗል። ለሃዋሳው ኤርፖርት ግንባታ ከዚህ በፊት በሸቤዲኖ ወረዳ ውስጥ ሞሮቾ ሾንዶላና ቀበሌ እና በኣከባቢው ያለው ቀበሌ ተመርጦ የነበረ ቢሆንም፤ በኣሁኑ ጊዜ ቦታው ተቀይሮ በሃዋሳ ዙሪያ ወረዳ ውስጥ ኡዶ ዎጣጤና ሳማ ኤጀርሳ ቀበሌ እንዲዛዎር ተደርጓል። እንደሪፖርተራችን ጥቻ ወራና ዘጋባ መሰረት የቦታ ለውጡ የተደረገው ከሞሮቾ ሾንዶላ ቀበሌ እና ከሌሎች በኣከባቢው ካሉ ቀበሌያት ለኤርፖርት ግንባታ ሲባል የምነሱ ሰዎች ቁጥር ብዙ በመሆኑ ለምነሱ ሰዎች እና ለመሬት ይዞታ ብሎም ለንብረት የምከፈለው ካሳ ከፍተኛ በመሆኑ መንግስት ለካሳ የምከፍለውን ገንዘብ ለማስቀረት ሌላ ኣማራጭ ቦታ መፈለግ የግድ ሰላሆነበት መሆኑ ታውቋል።