Posts

የሰሞኑ ዝናብ ያልተለመደ ነው

Image
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 28 ፣ 2006 ( ኤፍ.ቢ.ሲ ) የብሄራዊ ሚቲዮሮሎጂ ኤጀንሲ በአሁኑ ወቅት በመስከረም ወር እየጣለ ያለው ዝናብ ያልተለመደ መሆኑን ገለጸ ። በኤጀንሲው የሚቲዎሮሎጂ ትንበያና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ድሪባ ቆሪቻ እንደገለጹት ፥ ከባለፈው መስከረም 20 ጀምሮ አብዛኛውን የሃገሪቱን ክፍል የሸፈነ የዝናብ ስርጭት ተስተውሏል። ዳይሬክተሩ በተለይም በአማራ ፣ ኦሮሚያ ፣ ደቡብና ሃረሪ ክልሎች እንዲሁም በሶማሌ ክልል ሰሜናዊ አጋማሽ ድሬዳዋን ጨምሮ ይህ ያልተለመደ ዝናብ ያለማቋረጥ መዝነቡን እና በተለይም የአማራ መካከለኛው ምስራቅ ፣ ደቡብ ኦሮሚያ እና የደቡብ ክልል ሰሜናዊ አጋማሽ ከበድ ያለ ዝናብን  ያስተናገዱ አካባቢዎች እንደነበሩ ገልጸዋል ። ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ ግን ይህ የዝናብ ስርጭት በሃገሪቱ ሰሜናዊ ክፍለ የመቀነስ አዝማሚያ ማሳየቱን ነው አቶ ድሪባ የተናገሩት ። በተመሳሳይ በቀጣዮቹ አራት ቀናት ውስጥ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑትና በዚህ ወቅት ሰብል መሰብሰብ በሚጀምሩት  የሃገሪቱ ሰሜን ፣ ሰሜን ምስራቅና የስምጥ ሸለቆ አካባቢዎች የዝናብ ስርጭቱ እንደሚቀንስ አቶ ድሪባ አስረድተዋል ። የሜትዮሮሎጂ ትንበያ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት በደቡብና ደቡብ ምስራቅ የሃገሪቱ አካባቢዎች ደግሞ የዝናብ ስርጭቱ በመጠንም ሆነ በሽፋን እየተስፋፋ እንደሚሄድ ይጠበቃል ። ከዚህ ጋር በተያያዘ የወቅቱ ዝናብ ዘግይተው ለተዘሩ ሰብሎች ጥቅም ሊኖረው እንደሚችል ነው ሀላፊው የገለጹት። በቀጣይ ግን እንደባለፈው ሳምንት የተስፋፋ ዝናብ እንደማይጠበቅ ፥ ይሁንና በአንዳንድ ስፍራዎች ያልተጠበቀ ዝናብ ሊከሰት ስለሚችል የደረሱ ሰብሎችን በመሰብሰብ ረገድ አርሶ አደሩ ጥንቃቄ እንዲወስድ አሳስበዋል።

Student Transport Bedlam

Image
During the begging of academic years many of the universities call their students at the same time, which causes transport chaos and related problems on the students. Habtamu Asmamaw, 23, is a fourth-year law student at Dilla University, located in Dilla in the Southern regional state. He is 900km from his home town of Merawi, in the West Gojjam Zone of the Amhara Regional State, 33 km from Bahir Dar – the regional capital. During the last summer, however, he nearly reached boiling point, almost deciding not to return to his hometown. This was due to severe transport problems and other related issues that he witnessed on his way from Merawi to Dilla. “Last year, on our way to Dilla, we stopped at Bahir Dar’s bus terminal in search of transport. At that time, there was an acute transport shortage and a lot of chaos around the bus station,” Habtamu recalls. “Because of this chaos, some bags were stolen.” On Tuesday, October 2, 2013, Habtamu was at the larger intercity bus ter

New Agricultural Inputs Credit Directive to be Issued

Image
The new directive comes after research suggests that farmers have not substantially increased production after 30 years of fertiliser use Khalid Bomba, chief executive officer of Agricultural Transformation Agency and Nega Woubneh (PhD), senior director of Value Chain Programmes at the ATA.   A new directive that revises the old system of disbursing loans for agricultural inputs, such as fertiliser and seeds, is expected to be issued by the Ministry of Agriculture (MoA) in two months. The new system was developed in partnership with the Ethiopian Agricultural Transformation Agency (ATA) – an institution set up through funding by the Bill & Melinda Gates Foundation to identify bottlenecks in the agricultural industry and apply systemic solutions. Major contents of the draft directive were presented to stakeholders by Nega Woubneh (PhD), senior director of Value Chain Programmes at the ATA, on Thursday, October 3, 2013, at Hotel Siyonat. Changes made to the old system

‹‹በኢሕአዴግ ውስጥ መከፋፈል አለ የተባለው ምኞት ነው›› ተባለ

-የሃይማኖት አክራሪነት ትግል ፖለቲካዊ ነው አሉ  -የተቃዋሚዎች የሰላማዊ ሠልፍ ጥያቄ ከቀጠለ እንደሚቆም ገለጹ -በኬንያ የደረሰው ጥቃት በኢትዮጵያ ላይ እንደደረሰ ይሰማናል ብለዋል የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሕልፈት ተከትሎ በ2005 ዓ.ም. መስከረም ወር ላይ በይፋ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የተሾሙት አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የሥልጣን ቆይታ አንድ ዓመት አስቆጥሯል፡፡ የአንድ ዓመት የሥልጣን ቆይታቸው ከተቆጠረ ሁለት ሳምንታት በኋላ ባለፈው ዓርብ ለአገር ውስጥና ለውጭ የመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡  ይህ ጋዜጣዊ መግለጫቸው ወደ ሥልጣን የመጡበትን አንደኛ ዓመት ለማስታወስ ባይሆንም፣ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም በአኅጉራዊና በዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ በመስጠት ከጋዜጠኞች ለቀረቡ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል፡፡  በዋናነት ካነሷቸው ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዋነኞቹ በኢትዮጵያ የሃይማኖት አክራሪነትና ሽብርተኝነት፣ በኢሕአዴግ ውስጥ አለ ስለሚባለው አለመግባባትና የተቃዋሚ ፓርቲዎች በሰላማዊ ሠልፍ የሚያነሷቸው ጥያቄዎች ይገኙበታል፡፡ በኢኮኖሚ ረገድ የአገሪቱ ኢኮኖሚ በተጠናቀቀው ዓመትም ፈጣን ዕድገት ማስመዝገቡን፣ የግል ባለሀብቶች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው ዘርፎች ለመሳተፍ አለመፈለግ፣ መሠረታዊ በሚባሉት የመጠጥ ውኃ፣ የሞባይል ስልክና የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎቶች የሚስተዋሉ የአገልግሎት መቆራረጦች ሊቀረፍ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡  ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ጋዜጠኞች ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ዕድል ከመስጠታቸው በፊት ባለፈው የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አገሪቱ ስላስመዘገበቻቸው ውጤቶች አጠር ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በእሳቸው ማብራ

የመንግሥትን አስቸኳይ ትኩረትና መፍትሔ የሚሹ ሰባት ዓበይት ችግሮች

Image
ይበዛ ያንስ፣ ይሰፋ ይጠብ፣ ይረዝም ያጥር፣ ይሻል ይባስ እንደሆነ እንጂ ምንጊዜም በየትም አገር ችግሮች ይኖራሉ፡፡ ዋናው ጉዳይ ችግር መኖሩ አይደለም፡፡ ችግሩን ለይቶ፣ አውቆና ትኩረት ሰጥቶ መፍትሔ መስጠት ያለመቻል ካለ ነው የሚያሳስበው፡፡ መፍትሔ ያላገኘ ችግር እየተባባሰ ሄዶ አገርንና ሕዝብን ለአደጋ ይዳርጋልና፡፡  ይህ ስለሆነም ነው ሁላችንም እንደ ሕዝብና እንደ ዜጋ፣ በተለይም መንግሥት ኃላፊነት የተሸከመ አካል እንደመሆኑ መጠን በየጊዜው የአገር ችግሮችን እየመረመረ፣ እየገመገመና ቅደም ተከተል እያስያዘ ለችግሮች መፍትሔ መስጠት ይኖርብናል፡፡  በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያችን እንደሌላው አገር ሁሉ የተለያዩ ችግሮች አሉ፡፡ ተገቢውን ትኩረት ካላገኙና አስቸኳይ መፍትሔ ካልተደረገላቸው በአገር ላይ አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ ችግሮቹ ተለይተውና ታውቀው ልዩ ርብርብ ሊደረግባቸው ያስፈልጋል፡፡ የግድ ይላል፡፡ የመንግሥትን ትኩረትና መፍትሔ የሚሹ ወቅታዊ፣ ልዩና አስቸኳይ ዓበይት የኢትዮጵያ ችግሮች የምንላቸው የሚከተሉት ናቸው፡፡  1.ሰብሰብ፣ ጠንከርና ነቃ ያለ የመንግሥት አመራር ያስፈልጋል የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በሞት ሲለዩና አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሲሰየሙ ምንም ችግርና ብጥብጥ አልነበረም፡፡ ከዚያ በኋላም ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ አገራችን እየተመራች ናት፡፡ ይህን የሚመለከት ችግር ስላለ አይደለም ሰብሰብ፣ ጠንከርና ነቃ ያለ መንግሥትና አመራር ያስፈልጋል እያልን ያለነው፡፡ ዓለም በኢኮኖሚ ቀውስ እየታመሰ ነው፡፡ እኛንም እየጐዳን ነው፡፡ ትላልቅና በርካታ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ ሲደረጉ ከፍተኛ ፋይናንስ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ በፊት ያልነበረ የሃይማኖት ግጭትና ልዩነት እየታየ ነው፡፡ ችግሩ ካልተፈታ አስጊ ነው፡፡ የኢትዮጵያን ዕድገት የማይሹና