ሁላችንም ጉድለታችንን አውቀን ብናስተካክል ኖሮ ኢትዮጵያችን የትና የት በደረሰች ነበር?
ጉድለት መኖሩና ስህተት መፈጸም ምንጊዜም የትም ያለ ነው፡፡ ዋናው ጉዳይ ጉድለት ለምን ታየ? ስህተት ለምን ተፈጸመ? የሚለው አይደለም፡፡ ችግራችንንና ጉድለታችንን ዓይተንና መርምረን እናስተካክላለን ወይ? የሚለው ነው ዋናው ጉዳይ፣ ዋናው ቁም ነገር፡፡ መንግሥትም እንደ መንግሥት ጉድለት አለበት ስህተት ይፈጽማል፡፡ ገዥው ፓርቲም እንደ ገዥ ፓርቲ ስህተት ይፈጽማል ጉድለት አለበት፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ጉድለት አለባቸው ስህተት ይፈጽማሉ፡፡ የግል ዘርፉ ጉድለት አለበት ስህተት ይፈጽማል፡፡ ሲቪል ማኅበረሰቡም ጉድለት አለበት ስህተት ይፈጽማል፡፡ መገናኛ ብዙኃንም ስህተት ይፈጽማሉ ጉድለት አለባቸው፡፡ ግን! ነገር ግን! እነዚህ አካላት የራሳቸውን ስህተትና ጉድለት ያውቃሉ? ያያሉ? ወይስ በሌላው ስህተትና ጉድለት ላይ ብቻ ነው የሚያተኩሩት? የራሳቸውን ስህተት መረዳትና ማወቅ ብቻ ነው ወይስ ለማስተካከል ይጥራሉ? ይታገላሉ? የእኛ ፅኑ ዕምነት ሁላችንም ስህተታችንንና ጉድለታችንን ዓይተን፣ አውቀንና አምነን ብናስተካክል አገራችን የትና የት ትደርስ ነበር የሚል ነው፡፡ መንግሥት ከቃላት ባሻገር ከልብ በተግባር በመልካም አስተዳደር ላይ በተጨባጭ የሚታየው ጉድለትና ስህተት ምንድነው? ዲሞክራሲን እውን ለማድረግ፣ ሰብዓዊ መብት ለማክበር፣ ፍትሕ ለማንገስ፣ የፕሬስ ነፃነትን ዳር ለማድረስና ሙስናን ለማስወገድ ተጨባጭ ድክመቴ ምንድነው? ብሎ ለማወቅ ቢረባረብና ለማረም ቢታገል ትልቁ የአገር ችግር ይፈታል፡፡ አመቺ የሥርዓት ግንባታ ይዘረጋል፡፡ በሁሉም መስክ ታሪካዊ ለውጥ እውን ለማድረግ ጉዞው ቀላልና ብርሃን ይሆናል፡፡ ተቃዋሚዎች ራሳቸው የትም ይኑሩ የት በመንግሥት በኩል ያለውን ጉድለት ብቻ ለማየት ከመረባረብ ባሻገር ምን ዓይነት ጉድለትና ስህተ