Posts

በሀዋሳ ከተማ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ ተሰጠ

Image
አዋሳ ሐምሌ 10/2005 በሀዋሳ ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት ከ523 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 56 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ ለመግባት እየተዘጋጁ መሆናቸውን የከተማው ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ ገለጸ፡፡ በከተማው የዘንድሮን ሳይጨምር 5 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያላቸው ሌሎች ባለሀብቶች በፈጠሯቸው የስራ እድሎች ከ28ሺህ 600 ለሚበልጡ ዜጎች ተጠቃሚ ማድረጋቸውም ተገልጿል፡፡ በመምሪያው የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠት ፐርፎርመርና የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ወግደረስ ወንድሙ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በተጠናቀቀው የበጀት አመት ከ523 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል በማስመዝገብ ፍቃድ የወሰዱት 56 ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ፣ በኮንስትራከሽን ፣በሆቴልና ሌሎች ማህበራዊ አገልገሎቶች ለመሰማራት ነው፡፡ ባለሀብቶቹ በግላቸው ባላቸውና በጊዜዊነት በተሰጣቸው ቦታዎች በአሁኑ ወቅት ወደ ስራ ለመግባት በዝግጅት ላይ መሆናቸውና ስራ የጀመሩ እንዳሉ አመልክተው በሙሉ አቅማቸው ሲንቀሳቀሱ 2ሺህ ሰዎች የስራ እድል ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ለኢንቨስትመንት ልማት የሚውል 420 ሄክታር የሚጠጋ መሬት ዘንድሮ በጥናት ተለይቶ ለአልሚ ባለሀብቶች መዘጋጀቱንና ከዚሀም ውስጥ 270 ሄክታር በሀገር አቅፍ ደረጃ በማዕከላዊ መንግስት ለአንዱስትሪ ልማት የሚፈለግ ነው ብለዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለኢንዱስትሪ ልማት ከተመረጡ አምስት ከተሞች መካከል ሀዋሳ አንዷ በመሆኗ ማዕከላዊ መንግስት ከውጪና ከሀገር ውስጥ ለሚጋብዛቸው አልሚ ባለሃብቶች እንዲውል ያዘጋጁት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ቀሪው 150 ሄክታር መሬት በኢንዱስትሪ፣ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣በሪል ስቴትና በአገልግሎት ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብ

ሃዋሳን ጨምሮ የከተሞች ማስፋፍያ እና የኢኮኖሚ እድገት መርሀ ግብር ተግባራዊ ሊሆን ነው

Image
የከተሞች የተቀናጀ ማስፋፍያ እና የልማት መርሀ ግብርን ተግባራዊ ማድረግ በከተሞች አያደገ ለመጣው የመሬት አቅርቦት ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ እንደሚሰጥ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የከተሞች ማስፋፍያ እና አካባቢ ልማት መርሀ ግብር ማስጀመሪያ ወርክሾፕ እየተካሄደ ነው፡፡ የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር አቶ ሞክርያ ሀይሌ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በከተሞች መሰረተ ልማት፣ እድገት እና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትኩረት ያደረገ ስትራቴጂ ተግባራዊ ተደርጎ በከተሞቹ የማስፈፀም አቅምና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ውጤት የተገኘ ቢሆንም የተቀናጀ የከተሞች ማስፋፋትና የልማት ፕሮግራምን ውጤታማ ከማድረግ አንፃር ግን ብዙ መስራት ይጠበቃል ብለዋል፡፡ አሁን በኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ ድጋፍ አድራጊነት በሙከራ ደረጃ በአራት ከተሞች ላይ ተግባራዊ የሚደረገው የከተሞች ማስፋፊያ እና አከባቢ ልማት መርሀ ግብር ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚያግዝም ጠቁመዋል፡፡ መርሀ ግብሩ በፈጣን የከተሞች መስፋፋት እና የኢኮኖሚ እድገት ሳቢያ እያደገ ለመጣው የቤቶችና ኢንዱስትሪ ግንባታዎች የመሬት አቅርቦት እንዲኖር ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር ባለፈ የከተሞችን ገቢ በማሳደግ ረገድም ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሏል፡፡ መርሀ ግብሩ በሙከራ ደረጃ በአዳማ፣ ሀዋሳ፣ ባሀርዳር እና መቀሌ ከተሞች ላይ ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን በመጪው ጥር ወር ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ፅሕፈት ቤት ዘግቧል፡፡ http://www.ertagov.com

ሰለ ሲዳማ ቡና

Image
Ethiopian Distinct Coffee  Sidamma The region of Sidama is in southern Ethiopia. It encompasses many individual origins, including, geographically, the area of Yirgacheffe. However, Yirgacheffe is classified as its own separate origin. In this section, we discuss Sidama as a designated coffee origin. The name Sidama is often spelled "Sidamo," and the two names are generally used interchangeably. Some of the confusion comes from earlier political designations that called Sidama the large federal region which stretches from the town of Shashemene in the north all the way to the Kenyan border; and which called Sidama a much smaller sub-region which contains the towns of Hawassa (Awassa), Yirga Alem, and Dila. All the coffee origins designated as Sidama are within the larger territory of Sidama, but not all are within the smaller state of Sidama. To avoid confusion, it's best to just consider all the central-southern Ethiopian coffees as Sidama, and then use the spe

ዩኒቨርስቲው 26 አዳዲስ ፕሮግራሞችን ለመክፈት እየሰራ ነው

Image
ሃዋሳ ሐምሌ 8/2005 በድህረና ቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር ለ26 አዲስ ፕሮግራሞች ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ገለጹ፡፡ በዩኒቨርስቲው የሀዋሳ ግብርና፣ ህከምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተለያየ ሙያ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ መርሀ ግብር ያሰለጠኗቸውን ከ900 የሚበልጡ ተማሪዎች ትናንት አስመርቀዋል፡፡ የዩኒቨርሰቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ እንደገለጹት በተጠናቀቀው የትምሀርት ዘመን ለ18 አዳዲስ የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ስርዓተ ትምህርት ቀረጻ ተጠናቆ አንዳንዶቹ ተማሪዎችን ተቀብለው ለማስተማር እንቅስቃሴ ጀምረዋል፡፡ ከፕሮግራሞቹ መካከል አግሪ ቢዝነስና ቫሊዩ ቼን ማኔጅመንት፣ በባዮቴክኖሎጂ ፣በአግሮ ኢኮሎጂና ሰስቴነብል አግሪካልቸር ይገኙበታል፡፡ በህክምና ትምህርት ቤት ደግሞ በውሰጥ ደዌ፣ በሀጻናት ህክምና፣ በቀዶ ጥገና ፣ በማህጸን ጽንስ ስፔሻሊቲ የስልጠና ፕሮግራም ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ለመክፈት ዝግጅት መደረጉ ተመልክቷል፡፡ በቅድመ ምረቃ በቅርቡ ከተከፈተው የሲዳምኛ ቋንቋ በተጨማሪ ለ7 ፕሮግራሞች ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ በአንዳንዶቹ ተማሪዎችን ለመቀበል መዘጋጀታቸውን ዶክተር ዮሴፍ ጠቁመዋል፡፡ ይህም ዩኒቨርስቲው የቅበላ አቅሙን በመደበኛ ፕሮግራም ብቻ አሁን ያሉትን 17 ሺህ 080 ተማሪዎችን ቁጥር በ2007 ወደ 26 ሺህ ለማድረስ የተያዘው ፕሮግራም አንዱ አካል በመሆኑ ለዚህ ስኬት ከማስፋፊያ ግንባታዎች ባሸገር ቀልጣፋና ዘመናዊ አሰራር መዘርጋታቸውን ገልጠዋል፡፡ የመምህራንን አቅም በማጎልበት ረገድ በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ከ400 በላይ መምህራን በሀገር ውስጥና በውጪ የከፍተኛ ትምህርታቸውን እየተማሩ ይገኛል ብለዋል፡፡ በመንግስት የተጀመረው የልማት እንቅስቃሴ በጥናትና ምር

የደቡብ ክልል ምክር ቤት 7ኛ መደበኛ ጉባኤ ከ15 ነጥብ 4ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ

Image
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 07/2005 (ዋኢማ) - የደቡብ ክልል ምክር ቤት 7ኛ መደበኛ ጉባኤ ዘንድሮ በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ማስፈፀሚያ ከ15 ነጥብ 4ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ ፡፡  ምክር ቤቱ ያፀደቀው በጀትም ከቀዳሚው ዓመት ከ1 ቢሊዮን 480 ሚሊዮን ብር በላይ ብልጫ እንዳለውም ተገልጿል፡፡  የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይለብርሃን ዜና በጀቱን ለክልሉ ምክር ቤት ጉባኤ አቅርበው ባጸደቁበት ጊዜ እንደተናገሩት በጀቱ ለመሰረተ ልማት ፣ ለድህነት ተኮር ፕሮግራሞች፣ ለምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦችና ለመልካም አስተዳደር ስራዎች ማስፈጸሚያ ይውላል፡፡  ለክልሉ ከተመደበዉ በጀቱ ዉስጥ ከ8 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የሚበልጠው ከፌዴራል መንግስት የቀመር ጥቅል ድርሻ፣ ከ3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ከክልሉ ከተለያዩ የገቢ ምንጮች የሚሰበሰብ ሲሆን ከ3 ቢሊዮን 015 ሚሊዮን ብር በላይ ደግሞ ለምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ከፌዴራል መንግስት ድጋፍ የሚገኝ ነዉ ።  እንዲሁም ከውጭ ሀገራት ይገኛል ተብሎ ከሚጠበቀው ገንዘብ 6 ሚሊዮን 882 ሺህ ብር በብድር ፣ 116 ሚሊዮን 842 ሺህ ብር ከእርዳታ መሆኑን ተናግረዋል፡፡  አጠቃላይ ከተመደበው በጀት ውስጥም ለታችኛው የአስተዳደር እርከን በዓላማ የተገደበ በጀት 76 በመቶ ሲሆን ቀሪው 24 በመቶ ለክልሉ ቢሮዎች የተያዘ መሆኑን አቶ ኃይለብርሃን ገልፀዋል፡፡ የበጀት ክፍፍል ሲደረግ ትምህርት፣ ጤና፣ ግብርና ልማት ስራዎች፣ መስኖና የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታ፣ እንዲሁም የአስተዳደርና ሌሎች ሴክተሮች ወጪ በጥልቀት እንዲካተት መደረጉን አስታውቀዋል፡፡  የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ዴሴ ዳልኬ በሰጡት አስተያየትም የክልሉ በጀት የተደለደለዉ ህገ መንግስቱን መሰረት በማድረግ በፍ