የሚያዝያው ምርጫ ነጠላ አልበም - Quick Fix!
የመብራት ኀይል “ትራንስፎርመር” ተቃጠለ (ትራንስፎርሜሽኑስ?) ቴሌኮም “ሲምካርድ ከእኔ፤ ኔትዎርክ ከእናንተ” ቢለን ይሻላል ምርጫ ቦርድ “ምርጫው እንጂ ምህዳሩ አያገባኝም” ብሏል ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ የሞባይሌ ቴክስት ሜሴጅ (SMS) ድምፅ ነው፡፡ በጣም ተናደድኩኝ፡፡ ሰዓቱ እኮ ገና አንድ ሰዓት አልሆነም፡፡ ቀን ቀን በኔትዎርክ መጨናነቅ ከአገልግሎት ክልል ውጭ የሚሆነው ሞባይሌ በዚህ ሌሊት እንዴት ይረብሸኛል? ይሄኔ እኮ የራሱ የቴሌኮም ማስታወቂያ ይሆናል… ብዬ አሰብኩ፡፡ “የ100 ብር ካርድ ስትሞሉ 15 ደቂቃ ነፃ የአየር ሰዓት ታገኛላችሁ” የሚለው አይነት ማለቴ ነው (ፅድቁ ቀርቶብኝ በቅጡ በኮነነኝ!) ሌላ ሌላው ማትጊያ ቀርቶብን ኔትዎርክ ብናገኝ እኮ ይበቃን ነበር፡፡ አሊያም ደግሞ ሃቁን በይፋ ቢነግረን ቁርጣችንን እናውቀዋለን፡፡ “አያችሁ ከዛሬ ጀምሮ የኔትዎርክ ጉዳይ አይመለከተኝም፤ ሲም ካርድ ከእኔ፤ ኔትዎርክ ከናንተ” ቢለን እኮ አርፈን እንቀመጣለን፡፡ ወይም ኔትዎርክ ከቻይና እናፈላልጋለን ፡፡ ባለፈው ሳምንት በኢቴቪ በቀረበ የፓናል ውይይት ላይ የመብራት ሃይል ኮርፖሬሽንና የቴሌኮም ተወካዮች ከነዋሪዎች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችና ቅሬታዎች አጥጋቢ መልስ አጥተው ሲጨናነቁ አይቼ አፈርኩም አዘንኩም፡፡ አንድ አስተያየት ሰጪ ምን አሉ መሰላችሁ? “ለምን አልቻልንም ፤ ከአቅማችን በላይ ነው ብላችሁ እውነቱን አትነግሩንም? ስንት ዘመን ነው ይሄንን እየሰራን ነው… ያንን እያደረግን ነው የምትሉት!” ሲሉ አፋጠጧቸው፡፡ በነገራችሁ ላይ እቺ አባባል ለእነ ቴሌኮም ብቻ ሳይሆን ለእነኢህአዴግም ትሰራለች፡፡ አዎ አንዳንዴ እኮ ማመን አለባቸው (ስንት ዘመን በሽወዳ!) እናላችሁ --- እነኢህአዴግና ሌሎችም ሲያቅታቸው “አልቻልንም! ከአቅማችን በላይ ነው” ቢሉን ትልቅ ው