Posts

በመካከለኛው የኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ አካባቢ የነዳጅ ልማትና ፍለጋ ሊካሂድ ነው

Image
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 14፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) አፍሪካ ኦይል ኮርፖሬሽን በመካከለኛው የኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ አካባቢ የነዳጅ ልማትና ፍለጋ ሊያካሂድ ነው። የማዕድን ሚኒስቴርና ኩባንያው በፍለጋው ላይ ዛሬ የስምምነት ሰነድ ተመፈራርመዋል። በፊርማው ወቅትም የማዕድን ሚኒስትሯ ወይዘሮ ስንቅነሽ እጅጉ ነዳጅ ፈላጊ ኩባንያው በሃገሪቱ ጥናቶችን ሲያደርግ እንደመቆየቱና በሌሎች ሃገራትም ስኬታማ ስራዎችን እንደመስራቱ ፥  ፍለጋው ውጤታማ ይሆናል ብለን እናምናለን ብለዋል። የኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ጀምስ ፍሊፕስ ደግሞ በኢትዮዽያም ተስፋ ሰጪ ጥናቶችን አካሂደናል ወጤታማ እንደምንሆነም እምነታችን ነው ብለዋል ። ከቱሎው ኦይል ጋር በጋራ እያካሄድን ያለው ቁፋሮም በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ በመሆኑ በአጭር ጊዜ ውጤቱን እናሳውቃለን ብለዋል ። በእመርታ አስፋው

አሮሬሳ ወረዳ የ119 ሺህ 874 ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ከጃፓን መንግሥት ኣገኘ

Image
አዲስ አበባ የካቲት 13/2005 ጃፓን በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚካሄዱ የማኅበረሰብ ልማት ሥራዎች የሚውል ከ581 ሺህ ዶላር በላይ ለአራት መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ለሲዳማ ዞን አስተዳደር ዛሬ ድጋፍ አደረገች። የልማት ሥራዎችን ለማከናወን ከጃፓን መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ የተደረገላቸው በትግራይ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በሐረር ክልል ለሚገኙ የልማት ማኀበራትና ድርጅቶች እንዲሁም ለሲዳማ ዞን አስተዳዳር ነው። በድጋፍ የተገኘው ገንዘብ በአራቱ ክልሎች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ማኅበረሰቦች የትምህርት ቤቶች ማስፋፋያ፣ ንጹህ የመጠጥ ውኃ ግንባታና ለጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ግንባታ የሚውል ነው። የጃፓን መንግሥት በድጋፍ ከሰጠው ገንዘብ ውስጥ 122 ሺህ 229 ዶላር በከንባታ ጠንባሮ ዞን ውስጥ ለሙዱላ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ሲውል 119 ሺህ 874 ዶላር ደግሞ በሲዲማ ዞን አሮሬሳ ወረዳ ለሚገኝ ትምህርት ቤት ግንባታና ቁሳቁስ ማሟያ እንደሚውል ተገልጿል። እንዲሁም 118 ሺህ 575 ዶላር በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ለማንዱራ ወረዳ ለትምህርት ቤትና የአስተዳደር ቢሮ ግንባታ የሚውል ሲሆን 116 ሺህ 208 ዶላር ደግሞ በሐሪር ክልል ለድሬ ጢያራና ለሶፊ ወረዳ ለንጹህ የመጠጥ ውኃ ግንባታ ይውላል።  ቀሪው 104 ሺህ 689 ዶላር ደግሞ በትግራይ ክልል ለእንደርታና ለክልት አውላዕሎ ወረዳ ንጹህ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች ማከናወኛ የሚውል ሲሆን ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ ከ5 ሺህ በላይ አባወራዎችን ተጠቃሚ ያደርጋሉ። በኢትዮጵያ የጃፓን ኤምባሲ ጉዳይ አስፈፃሚ ሚስተር ሃጂሜ ኪታኦካ በኤምባሲው በተካሄደው የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት የትምህርት ተቋማቱና የንጹህ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች ግንባታ ሲጠናቀቅ በአጠቃላይ ከ15 ሺህ በላይ የአካ

የክልሉ ምክር ቤት ሶስተኛ ዓመት አራተኛ ዙር ስድስተኛ መደበኛ ጉባኤ በሃዋሳ ከተማ እንደቀጠለ ነው

Image
በደቡብ   ብሄር   ብሄረሰቦችና   ህዝቦች   ክልል   በበጀት አመቱ   አጋማሽ   በየዘርፉ የተከናወኑ   ተግባራት   አበረታች   ውጤት   የተመዘገበባቸው   መሆኑን   የክልሉ   ርዕሰ መስተዳድር   አስታወቁ   ። የክልሉ   ምክር   ቤት   ሶስተኛ   ዓመት   አራተኛ   ዙር   ስድስተኛ   መደበኛ   ጉባኤ   በሃዋሳ ከተማ   እየተካሄደ   ነዉ   ።ርዕሰ   መስተዳድሩ   አቶ   ሽፈራው   ሽጉጤ   የክልሉን   የግማሽ በጀት   ዓመት   የዕቅድ   አፈጻጸም   ሪፖርት   ለምክር   ቤቱ   ባቀረቡበት   ወቅት   እንዳሉት  በየስራ   ዘርፉ   ካለፈዉ   ዓመት   ክንውን   ምርጥ   ተሞክሮዎችን በመውሰድና   በማስፋት   ስትራተጂ   በመጠቀም   ውጤታማ   ተግባራት   ተከናውነዋል   ። በመንግስትና   በህብረተሰቡ   የተሟላ   ተሳትፎ   የኪራይ   ሰብሳቢነትን   ችግሮችን   ለመቅረፍ   በሚያሰችል   መልኩ   በገጠርና   በከተማ   የተለያዩ   ተግባራትን በማከናወን   ለውጥ   ማምጣት   የተቻለ   መሆኑን   አስታዉቀዋል   ። ባለፉት   ስድስት   ወራት   በግብርና   ልማት፣   በመንገድ   ግንባታና   በቀበሌ   ተደራሽ   መንገድ   ስራዎች   የገጠር   ቀበሌዎችን   ዕርስ   በዕርስና   ከዋና   መንገድ ጋር   በማገናኘት  705  ኪሎ   ሜትር   መንገድ   ተገንብቶ   መጠናቀቁን የገለፁት አቶ ሽፈራው በዚህም   አርሶና   አርብቶ   አደሩ   ምርቱን   ለገበያ   በማቅረብ ተጠቃሚ   መሆኑን   አመልክተዋል   ። መንገዶቹ   በሚገነቡባቸው   አካባቢዎችም   በማህበር   ለተደራጁና   በጉልበት   ሰራ   ለተሰማሩ   ከ 106  ሺህ   በላይ   ሰዎች   የስራ   ዕድል   መፈጠሩን

Ethiopia: Yougovia With Vibe From Hawassa

Image
The interior of the new club, Yougovia, is spacious and painted with vibrant colors. It was on January 26, 2013 that Yougovia Club and Lounge came to the Addis Abeba night club scene after much preparation. The first branch located in Hawassa, 273Km from the capital, opened 13 years ago, and is still going strong. The success and the popularity gained there, made it possible to open a second branch in the basement of Sheger Building on Namibia Street near Bole Medhanealem. The owner, Birhan Tedla, named the club "Yougovia" from a story his brother-in-law told him, of how when the Italians left Mehal Meda in Amhara Region, they said yougovia, we leave you even as we love you. Historical accuracy aside, Birhan fell in love with the word and made it the name for his first night club in Hawassa. Birhan has other businesses including Oasis International Hotel, a 40 bedroom three-star hotel, which he established with a capital of 30 million Br along Lake Hawassa, and

ተቋርጦ የነበረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ (መለስ ዋንጫ) የፊታችን እሁድ ይጀመራል፤ በ9 ሰኣት ሲዳማ ቡና ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ይጫወታል

Image
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 12 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) ላለፉት ሁለት ወራት በአፍሪካ ዋንጫ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ (መለስ ዋንጫ) የፊታችን እሁድ ይጀመራል። በዚህም መሰረት እሁድ አዲስ አበባ ላይ ፥ የአምናው ሻምፒዮን ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመከላከያ በ9 ሰአት  እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና ከ ደደቢት በ11 ሰአት የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ክልል ላይ በሚደረግ ጨዋታ በይርጋአለም ስቴዲየም ፥ በ9 ሰአት ሲዳማ ቡና ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚጫወቱ ሲሆን ፥ አርባ ምንጭ ላይ ደግሞ አርባ ምንጭ ሃረር ቢራን በተመሳሳይ ሰአት ያስተናግዳል። መብራት ሃይል ከሙገር ሲሚንቶ ፣ ኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት ከኢትዮጵያ መድን የሚገናኙባቸው ጨዋታዎች የካቲት 21 የሚደረጉ ይሆናል። http://www.fanabroadcasting.com/index.php?option=com_content&view=article&id=2446:2013-02-19-13-43-22&catid=102:slide