Posts

አሥራ አምስት የመንግሥት ሆስፒታሎች የልቀት ማዕከል ሊሆኑ ነው

በታደሰ ገብረ ማርያም በመላ አገሪቱ የሚገኙና በአጠቃላይ የ15 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ የነበሩ 15 ምርጥ የመንግሥት ሆስፒታሎችን ከፍተኛና ጥራት ባለው የሕክምና ቴክኖሎጂ በማደራጀት፣ የልቀት ማዕከል እንዲሆኑ የማድረግ እንቅስቃሴ በመከናወን ላይ መሆኑ ታወቀ፡፡ እስካሁን በተካሄደው እንቅስቃሴ አዲስ አበባ ከተማ ለሚገኝ አንድ ምርጥ ሆስፒታል ኤምአርአይ የተባለ ዘመናዊ የሕክምና መሣርያ የቀረበለት መሆኑን፣ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የሜዲካል ሰርቪስ ዳይሬክቶሬት ምንጮች አስታውቀዋል፡፡ ምንጮች በተለይ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የትኛውንም የአካል ክፍል ጥራት ባለው ምስል የሚያሳየው የተራቀቀ ቴክኖሎጂ የቀረበውም ለቅዱስ ጳውሎስ ስፔሻላይዝድ አጠቃላይ ሆስፒታል ነው፡፡ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ሌሎችም ምርጥ ሆስፒታሎች አቅም በፈቀደ መጠን በየተራ የዚሁ የተራቀቀ ቴክኖሎጂ ባለቤት የሚሆኑበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን ተጠቁሟል፡፡ በመላ አገሪቱ ከሚገኙ 119 የመንግሥት ሆስፒታሎች መካከል፣ 15ቱ ብቻ ምርጥ ተብለው ሊለዩ የቻሉት የተለያዩ ደረጃዎች ያሉትና የተገልጋዩን እርካታ ማዕከል ያደረገ መስፈርት በማውጣት መሆኑን ምንጮች ጠቅሰው፣ የመጀመርያው መስፈርት የሆስፒታሎቹን አገልግሎትና የአፈጻጸም ሁኔታን የሚመለከት መሆኑንና በመስፈርቱ 30 ሆስፒታሎች መመረጣቸውን አስረድተዋል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው መስፈርት ተግባራዊ የሆነው የሰላሳዎቹን ሆስፒታሎች የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥን በአካል ተገኝቶ በማየትና በመገምገም ሲሆን፣ በዚህ ዓይነቱም አካሄድ 15 ሆስፒታሎች የሚፈለገውን ደረጃና መስፈርት አሟልተው በመገኘታቸው፣ ‹‹ምርጥ ሆስፒታሎች›› ተብለው መመረጣቸውን ከምንጮች ማብራሪያ ለመዳት ተችሏል፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ትብብር ለጥራት›› በሚል ፕሮጀክት አማካይነት መስፈር

መንግሥት ኢሕአዴግንና የንግዱን ኅብረተሰብ ያጣመረ የንግድ የልማት ሠራዊት ሊፈጥር ነው

በዳዊት ታዬ የንግድ ኅብረተሰቡ የሚጠበቅበትን አገራዊ አስተዋጽኦ እንዲወጣ ለማድረግ መንግሥት፣ ኢሕአዴግራና የንግዱን ኅብረተሰብ ያጣመረ የንግድ ልማት ሠራዊት መፍጠር የግድ ነው ሲሉ የንግድ ሚኒስትሩ አስታወቁ፡፡ የንግድ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔ ይህንን የገለጹት ትናንት በተካሄደው የመንግሥትና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ ነው፡፡ በሦስቱ ጥምረት ይመሠረታል የተባለው የንግድ የልማት ሠራዊት አገሪቱ ለጀመረችውና ተግባራዊ በማድረግ ላይ ላለችው ዕቅድ መሳካት ቁልፍ ሚና ይኖረዋል በማለት ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ የንግድ የልማት ሠራዊት መፍጠርን በተመለከተ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ፣ በሌሎች ዘርፎች እየተፈጠሩ እንዳሉት የልማት ሠራዊቶች ዓይነት አደረጃጀት እንዲኖረው ይደረጋል፡፡ ልማታዊ አስተሳሰብ እንዲኖር ሚኒስቴሩ የንግድ አሠራር ለውጥ እያደረገ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ከበደ፣ የንግድ ኅብረተሰቡን ከሚመለከቱ ሁለት ፓኬጆች ጐን ለጐን የንግድ ልማት ሠራዊት ለመፍጠር ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡ ‹‹በተደጋጋሚ በመገናኛ ብዙኅን እንደምትሰሙት በሦስት አካላት የሚመሠረት ነው፤›› ያሉት የልማት ሠራዊት ጥምረት የሚፈጠረው ‹‹ከገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ፣ ከመንግሥትና ከሚመለከተው የኅብረተሰብ ክፍል ነው፤›› ካሉ በኋላ፣ ‹‹በዚህ ጥምረት መንግሥትን የሚወክለው ንግድ ሚኒስቴር ነው፡፡ ከንግድ ሚኒስቴር አንፃር ሊፈጠር የታሰበው የንግድ ልማት ሠራዊት መንግሥት፣ ኢሕአዴግንና የንግድ ምክር ቤቶችን በጋራ እንዲሠሩ ዕድል ይፈጥራል፤›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ይህም በመግባባትና በመመካከር የሚፈለገውን ወጤት ለማስመዝገብ የሚያስችል መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ ዘመን ማጠቃለያ የንግዱ ዘርፍ 10.47 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማስገኘት የሚጠበቅበት መሆኑ

“ቦተሊካ”ና ነጻ ነገር…

Written by  ኤፍሬም እንዳለ እንዴት ሰነበታችሁሳ! ለእስልምና ተከታዮች በሙሉ ኢድ ሙባረክ! ይመቻችሁማ! እኔ የምለው…የእነኚህ፣ አለ አይደል…”ሪሞት ኮንትሮሉን” ይዘውብናል የሚባሉት አሳዳሪዎቻችን የምርጫ ክርክር አሪፍ አይደል! እንደዛ ልክ ልካቸውን “አጠጥተውና ጠጥተው” ሲተቃቀፉ ማየት መአመት ነገር እንድትናፍቁ አያደርጋችሁም! እኛ አገር እኮ…አለ አይደል…አይደለም “ቦተሊከኞች”፣ ኳስ ተጫዋቾች እንኳን የጨዋታው መጨረሻ ፊሽካ ሲነፋ ጀርባቸውን አዙረው ወደ መልበሻ ቤት አይደል እንዴ የሚሄዱት!እናማ…”ቦተሊከኞች” በሆዳቸው “እንዲህ ብለኸኝማ፣ የተወለድክበትን ቀን ባላስረግምህ…” ምናምን አይነት እየዛቱ የሚሄዱ ነው የሚመስለው፡፡ ድሮም እንዲያው ነን…ዘንድሮ ደግሞ ብሶብናል፡፡  ስሙኝማ…የዘንድሮ “ቦተሊከኝነት” ለምን ይናፍቅሃል አትሉኝም…ነፃ “ፉድና ድሪንክ”! ልጄ ቀላል ግብዣ አለ እንዴ! ወላ አሮስቶ ዲቢቴሎ፣ ወላ ስቴክ በያይነቱ፣ ወላ ስቶሊችኒያ…ምን አለፋችሁ የሦስተኛው ዓለም “ቦተሊከኛ” ዝም ብሎ በባዶ ሜዳ ፊቱ የቅቤ ቅል የሚሆን አይምሰላችሁ! በ “ፍሪ ፉድ”ማ እኛም ቅል (የቤውን ለማለት ነው፡፡ ቂ…ቂ…ቂ…) የማንመስልሳ! ኮሚክ እኮ ነው…ዘንድሮ ነፍስ ያለው ምግብ በመጽሔት ማስታወቂያና በአረብ ሳት ጣቢያዎች ላይ ብቻ እያየን…በ’አቋራጭ የሚበላበትን የማንመኝሳ! እናማ…አንዳንዴ የግብዣውን ብዛት ስታዩ…አለ አይደል…አንዳንድ ቦሶች “እሺ፣ ጤፍ ለምን፣ ለምን ያገለግላል?” ተብሎ ይጠይቁ፡፡ ምን አለ በሉኝ፣ አንዳንዶቹ…ለአርባ አራት ደቂቃ ካሰቡ በኋላ ትዝ ብሏቸው…”እሱ ነገር አሁንም አለ እንዳትሉኝ!” ባይሉ ምን አለ በሉኝ፡፡ (“ከምላሴ ፀጉር…” መባባል የቀረው ምላሳችን ፀጉር ባይኖረውም “በመኮሰኮሱ” ነው እንዴ!) ኑሮ እንዲህ የሆረር ፊልም በ

ኣቶ ፍሬህይወት ሳሙኤል የተባሉ የቀድሞ የደቡብ ክልል ክፍተኛ ፍርድ ቤት ኃላፊ እና ዳኛ ሰሞኑን ከኣራምባ ታምስ ጋር ስለሲዳማ እና ወላይታ ህዝብ በተመለከተ የሰጡትን ቃለ ምልልስ በተመለከተ የተሰጠ ምላሽ

A Personal Response to Irresponsible Interview Made by “Judge” Firehiwot Samuel with Awrabatimes on October  24/2012   The so called ‘Judge’Firehiwot, I know that had been head of High court in SNNPRG until you left Ethiopia three years ago. I do not know your educational background, but I had chance to know you in Hawassa and we both left Ethiopia behind in four months apart. As long as I know you, you are one of those cadres who were chewed like a gum, once turned sour or useless, spited out.  That is what happens to idiots like you in Ethiopian politicswho make decision through political and personal will rather than principles of universal accepted law. What interests me in this interview is the part you spoke on the issues of Hawassa, conflict between Sidama and Wolayta Nationals and your relationship with Haile Mariam Desalegn, the current prime minister of Ethiopia. You lamented on Hawassa: “Hawassa was Sidama administration center and at the same time SNNPRG capital, but

-Ethiopia:Joint Press Release: Sidama and Oromo National Youth Movements

Image
Joint Press Release Sidama and Oromo National Youth Movements The oppressed peoples in Ethiopia have spent years of painful struggle against alien’s domination and dictatorship. To this end, the struggles of the Sidama and Oromo peoples have already costed countless lives and a great deal of material destruction. Based on this foundation and fact, we, the Youth Representatives of the Oromo and Sidama peoples, have met from 24th-26th October 2012 and discussed on a wide range of matters concerning our peoples and the need for a common struggle against the common enemy. We have noted the current TPLF government’s deliberate impoverishment, looting, exiling, confiscation of land and unlawful imprisonment being unleashed against the Oromo and Sidama peoples. After long deliberation, we have agreed on the need to keep the struggle inherited from our struggle’s heroes and the need to realise them. Accordingly, we have agreed: 1.  To work together to realise our freedom an