Posts

ኢትዮጵያ ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፈውን የኤች.አይ.ቪ/ስርጭት ስርጭት ለመግታት ብዙ መሥራት ይጠበቅባታል

Image
አዲስ አበባ ጥቅምት 17/2005 ኢትዮጵያ ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፈውን የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ቫይረስ ስርጭት በመግታት ረገድ ብዙ መሥራት እንደሚጠበቅባት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡  ቢሮውና ኢንትራ ሄልዝ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ከእናት ለእናት አመቻች ቡድን ጋር በመስራት ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ከእናት ወደ ልጅ /ጽንስ/ እንዳይተላለፍ በተሰጠው አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ የ200 ሕጻናት እናቶች ዛሬ የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል፡፡  የቢሮ ኃላፊዋ ወይዘሮ ፋንቱ ጸጋዬ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭትን በመከላከል ውጤታማ እየሆኑ ከመጡ ጥቂት አገሮች አንዷ ብትሆንም፤ ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፈውን ስርጭት ለመከላከል የተጠናከረ እንቅስቃሴ ማድረግ ያስፈልጋል። በአሁኑ ወቅት ቫይረሱ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ በመግታት ረገድ ያለውን ክፍተት ለመድፈን በዓለም አቀፍ ደረጃ በሕጻናት ላይ የሚኖረውን የቫይረሱን አዲስ ስርጭት ሙሉ ለሙሉ ለማስቀረት የተያዘውን እቅድ በመቀበል ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ እንደምትገኝ ጠቁመዋል፡፡  የእቅዱ መተግበሪያ ዋነኛው መንገድም እናቶች በእርግዝና ወቅት ምርመራ እንዲያደርጉና ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ከሆነም አስፈላጊውን ሕክምናና የምክር አገልግሎት አግኝተው መከላከያ በመውሰድ ከቫይረሱ ነፃ የሆነ ሕጻን እንዲወልዱ ማድረግ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ለዚህም የጤና ተቋማትን ማስፋፋትና በሁሉም ተቋማት አገልግሎቱ እንዲሰጥ ማድረግ ወሳኝነት እንዳለው ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ በዚሁ መሠረት ከተማዋ የነበሯትን የጤና ጣቢያዎች ቁጥር በማሳደግና አገልግሎቱን በማጠናከር ሰፊ ሥራ መከናወኑንና በግል ጤና ተቋማት ጭምር አገልግሎቱ መስፋፋቱን አመልክተዋል፡፡ የጤና ተቋማቱን ቁጥር ወደ 11

ኢሕአዴግ ቆራጥና ደፋር የውስጥ ትግል ያስፈልገዋል

Image
ኢሕአዴግ በሕዝብ ተከብሮና ተደግፎ ጠንካራ መሠረት ይዞ ለመቀጠል ከፈለገ ይችላል፡፡ የሚችለው ግን ራሱን ሲያጠናክር ነው፡፡ ራሱን ማጠናከር የሚችለው ደግሞ ውስጡን ሲያፀዳ ነው፡፡ ውስጡን ማፅዳት የሚችለው ደግሞ ቆራጥና ደፋር የውስጥ ትግል ሲያካሂድ ነው፡፡ ደፋርና ቆራጥ የውስጥ ትግል ካካሄደ ፀድቶና ተጠናክሮ ይወጣል፣ ይቀጥላል፣ ይጓዛል፡፡ የለም አላደርግም፣ አልታገልም፣ አልቆርጥም፣ አልደፍርም ካለ ደግሞ ውስጥ ለውስጥ እየተሰነጣጠቀ፣ እየበሰበሰና እየተደረመሰ ይሄዳል፡፡ ይደክማል ከሕዝብ ይርቃል፡፡ የነበረው እንዳልነበረ ይሆናል፡፡ ኢሕአዴግ ቆራጥና ደፋር የውስጥ ትግል የሚያስፈልገው ለምንድን ነው? 1.    ከላይ እስከታች በሙስና የተጨማለቁ በዝተዋል! አዎን ንፁኃን የሕዝብ አገልጋይ፣ ለልማትና ለለውጥ የቆሙና የሚታገሉ አባላትም አመራርም በኢሕአዴግ ውስጥ አሉ፡፡ በዚያው አንፃር ደግሞ ከሕዝባዊ መስመር እየራቁና እየሸሹ ለግል ገንዘብ፣ ንብረት፣ ክብርና ኔትዎርክ የሚሯሯጡ፣ በጉቦ የተጨማለቁና በሙስና የተነከሩ አሉ፡፡ እነዚህ በውስጥ ትግል፣ በደፋርና በቆራጥ ትግል ካልተገለሉና ድርጅቱ ካልፀዳ ድርጅቱን እያበሰበሱ የሚገድሉት ናቸው፡፡ 2.    አቅም አልባ… ምላስ  ብዙ በዙ! በብቃት መመደብ እየቀረ ደጋፊ እስከሆነ ችግር የለም እየተባለ የተሾመው ሁሉ የድርጅቱን ዓላማ ማራመድ አልቻለም፡፡ ሕዝቡንም ማገልገል አልቻለም፡፡ ባለአቅም እየጠፋ ባለምላስ በዛ፡፡ ተንዛዛ በጣም በዙ፡፡ ሕዝብ ይህንን እያየና እያስተዋለ ምንድን ነው ነገሩ? እያለ ነው፡፡ አይወስኑም፣ ቢሮ አይገቡም፣ አያሳምኑም፡፡ አንዳንዶቹም ይህን እያወቁ ሀቅን ከመጋፈጥ ይልቅ ሽሽትና ድብብቆሽ እየመረጡ ናቸው፡፡ ሕዝብ በድርጅቱ ላይ አመኔታ እንዲያጣ እያደረጉ ናቸው፡፡ 3.    ጠንካራ አን

Beyond the Politics: - A look at a Reality of Sidama Economy

Image
By Kinkino Kiya, October 25, 2012 According to the most recent World Bank’s report that analysis the World poverty index; Ethiopia by all measures remains one of the poorest countries of the world. The most critical challenge facing the Sidama authorities and the Ethiopian policy makers at large -today and for the years ahead is the urgent task of reducing absolute poverty from the Sidama region as well as for the federal authorities addressing the issues at a national level. The basic objective of economic resources management and the fundamental goal of government anywhere, at all times must be working towards improving the standard of living of their respective people’s over time in the given periods of time. [...] The numerous Ethiopians including the Sidama nation were so optimistic trusting that the current might declare war on the greatest enemy of our people, the abject poverty that has incarcerated the nation of the country with varying degrees. Regardless of the a

ድህነትን ታሪክ ለማድረግ የተቀናጀ ዘመቻ

Image
ተስፋዬ ለማ ከዛሬ አራት ቀን በፊት ማለትም ጥቅምት 2/2005 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አጀንዳ አምድ በዚሁ ርዕስ ከታላላቅ የሀገራችን ልማት ሥራዎች የስኳር ልማት ፕሮጀክት እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረ ጽሑፍ ማቅረባችን ይታወሳል። በጽሑፉ በአገራችን በመስፋፋትና በመገንባት ላይ ያሉ ነባርና አዳዲስ የስኳር ልማት ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያ የምትመራ በትን የግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለማሸጋገር የሚያስችል መሠረት ለመጣል ከተያዙ ታላላቅ ሀገራዊ የኢንዱስትሪ ልማቶች በዋናነት የሚጠቀሱ መሆኑን ዳስሰናል።  በአምስት ዓመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መሠረት ነባሮቹን የማስፋፋትና አዳዲሶች የመገንባት አቅጣጫ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን ለማየትም ተሞክሯል። ከእዚሁ ጋር ተያይዞ የአገሪቱ የስኳር ፍላጎት ከሚመረተው ምርት ጋር ባለመጣጣሙ መንግሥት ከተለያዩ አገራት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ስኳር እያስገባ መሆኑን ጠቁመን ከሦስት ዓመታት በኋላ ግን አገሪቱ የሕዝቧን የስኳር ፍላጎት አሟልታ የተረፈውን ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተሻለ የውጭ ምንዛሪ የምታስገባበት ሁኔታ እንደሚፈጠር አይተናል።  ከስኳር ልማት ፕሮጀክቶቹ ጋር ተያይዞ በተለያዩ ወገኖች የሚነሱ መሠረት የለሽ አሉታዊ ዘገባዎች የአገራችንን የልማት አቅጣጫ ለማስቀየስ እንጂ መሠረታዊ ጠቀሜታ ኖሯቸው እንዳልሆነና በአሁኑ ወቅት ልማታችንን ለማደናቀፍ የሚሰነዘሩ አሉባልታዎችን የሚሰማ ጆሮ ያለው ኢትዮጵያዊ አለመኖሩንም ለማስገንዘብ ተሞክሯል። የኢትዮ ጵያ ሕዝብ ዋነኛ ጠላት ድህነት መሆኑን መግባ ባት ላይ መደረሱንም ነው በመጀመሪያው ጽሑፍ የቃኘነው።  በዛሬው ጽሑፍ በሀገራችን እየተገነቡ ካሉ አዳዲስ የስኳር ልማት ፕሮጀክቶች የወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክትን እንመለከታለን።  የወልቃይ

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የቡና ጉባኤ ሊካሄድ ነው ለውጭ ገበያ ከሚቀርበው ቡና 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ እንደሚገኝ ይጠበቃል

Image
አዲስ አበባ ጥቅምት 16/2005 በቡና ንግድ ዘርፍ መላው ባለድርሻ አካላትን የሚያሳትፍ የመጀመሪያው ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ በቅርቡ አዲስ አበባ ውስጥ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ኮፊ ኤክስፖትርስ አሶሴሽን አስታወቀ፡፡ ኢትዮጵያ ዘንድሮ ለዓለም አቀፉ ገበያ ከምታቀርበው የቡና ምርት 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ እንደምታገኝ ይጠበቃል፡፡ የአሶስዬሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ኦፊሰር አቶ ጌታቸው አድማሱ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጸው ጉባኤው የቡና ምርቶች መገኛ የሆነችውን ኢትዮጵያን ገጽታን ከመገንባት ባሻገር የተለያዩ ምርቶቿን ለዓለም አቀፉ ገበያ ለማስተዋወቅ የሚረዳ ነው፡፡ አሶስዬሽኑ ጉባኤውን በሚቀጥለው ሳምንት በአዲስ አበባ ሒልተን ለማካሄድ ከንግድ ሚኒስቴርና ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑንና በአሁኑ ወቅትም አስፈላጊውን ቅድም ዝግጅት በማጠናቀቅ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ለሁለት ተከታታይ ቀና በሚካሄደው ዓለም ዓቀፍ የቡና ጉባኤም 250 ሰዎች እንደሚሳተፉ ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ ጌታቸው ገለጻ ከአገር ውስጥ በቡና ንግድ የተሰማሩ ላኪዎችና አቅራቢዎች ድርጅቶች፣ የሕብረት ስራ ማህበራት ዩኒየኖችና የክልል ግብርና ቢሮ ተወካዮች፣ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅት ተጠሪዎችና የገንዘብ ተቋማት ይሳተፋሉ፡፡ በተጨማሪም ከውጭ ዓለም ዓቀፍ የቡና ገዢዎች፣ ቆይና ቸርቻሪዎች የጉባኤው እድምተኞች ይሆናሉ፡፡ በጉባኤውም በተለይ በቀጣዩ አውሮፓውያን ዓመት የኢትዮጵያ ቡና ምርት የውጭ ገበያ አቅርቦት በሚያድግበት እንዲሁም አገሪቱ ከዘርፉ የምታገኝው የውጭ ምንዛሪ ገቢም በዚያው ልክ የሚጨምርበት ሁኔታ በመምከር አዎታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ በዓለም ዓቀፉ ገበያ የኢትዮጵያ የቡና ወጪ ንግድ አቅርቦት አሁን ካለበት መጠ