Posts

ሲዳሙ ኣፎ ጭምሮ በ25 ቋንቋዎች የትምህርት መዛግብተ ቃላት እየተዘጋጁ ነው

ሐዋሳ (ኢዜአ)፡- የትምህርትን ጥራት በየደረጃው ለማረጋገጥ መንግሥት የሚደርገውን ጥረት ለማገዝ በኢትዮጵያ 25 የብሔረሰብ አፍ መፍቻ ቋንቋዎች የተጀመረው የትምህርት መዝገበ ቃላት ዝግጅት በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡ የመዝገበ ቃላቱ ዓላማና አስፈላጊነት ላይ ግንዛቤ ለማስጨበጥ በደቡብ ክልል ደረጃ የትምህርት ባለሙያዎች የተሳተፉበት የሁለት ቀናት አውደ ጥናት በሀዋሳ ከተማ ተካሄዷል፡፡ መዝገበ ቃላቱ እየተዘጋጀ ያለው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ20 ዓመታት በላይ የማስተማር ልምድና ዕውቀት ባላቸው ምሁራን ከሁለት ዓመት በፊት በተቋቋመው ስፖትላይት የትምህርት ማበልጸጊያ ማዕከል በተባለ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ትብብር መሆኑ ተገልጿል።  የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ አህመዲን በአውደ ጥናቱ ላይ እንደገለጹት የትምህርት ጥራትን በየደረጃው ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት የትምህርት መፃሕፍት ግብአት አቅርቦት አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑን አስታውቀዋል። በክልሉ 14 ቋንቋዎች ሳቢና ማራኪ አቀራራብ ለህጻናት አመቺ በሆነ መልኩ ከተዘጋጁት የትምህርት መጻህፍት መካከል በ10 የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች የቀረቡት በዝርዝር ታይተው ወደ ተግባር እንዲሸጋገሩ ተደርጓል ብለዋል፡፡  በአሁኑ ወቅት የደቡብ ክልል ቋንቋዎችን ጨምሮ በሀገር ደረጃ በ25 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች እየተዘጋጁ ያሉት የትምህርት መዘገበ ቃላት የትምህርትን ጥራት ለማስጠበቅ አስተዋጾኦ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ የማዕከሉ ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ብርሃኑ ቦጋለ እንዳስረዱት በኢትዮጵያ 25 ቋንቋዎች የትምህርት መዝገበ ቃላት መዘጋጀተው ለትምህርት ጥራት ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ከተማሩ በኋላ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ለመማር እንደሚገ

በመከላከልን መሠረት ያደረገውን የጤና ፖሊሲ ውጤታማ ለማድረግ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በተሠራው ሥራ በህብረተሰቡ ጤና ላይ ለውጥ መታዩተን የዳራ ወረዳ ጤና ፅህፈት አስታወቀ::

Image
በመከላከልን መሠረት ያደረገውን የጤና ፖሊሲ ውጤታማ ለማድረግ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በተሠራው ሥራ በህብረተሰቡ ጤና ላይ ለውጥ  መታዩተን የዳራ ወረዳ ጤና ፅህፈት አስታወቀ:: የጽህፈት ቤቱ በሽታ መከላክልና ጤና ማጎልበት ኦፊሰር አቶ ማቲዎስ ማልኬ እንደተናገሩት ለጤና ኤክስቴንሽን ባሙያዎች የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት የጤና ፓኬጁን ተግባራዊ ለማድረግ በ1 ለ5 ትሥሥር የጤና ልማት ሠራዊት በመገንባት በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ገልጸዋል:: አቶ ማቲዎስ አክለውም ተላላፊ በሽታን ለመከላከል የኅብተተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ እንደሚገባ ጠቅሰው በክረምት ወቅት ለሚከሰቱ የተለያዩ በሽታዎች አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል:: የወረዳው ዘርፈ ብዙ ኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና ማስተባበር ዋና የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ሙሉነህ ኪአሞ በበከኩላቸው በወረዳው የኤች አይቪ  ምርመራ የሚያደርጉ ሰዎች ቁጥር መበራከት ከታዩ  ለውጦች እንደ አብነት የሚጠቀሰ ነው ብለዋል፡፡ ሲል አዳነ አለማየሁ ከበንሳ ቅርንጫፍ ጣቢያ ዘግቧል:: http://www.smm.gov.et/_Text/23HamTextN104.html

በ2005 ለሚካሄደው የአካባቢ ምርጫ ለምርጫ አስፈፃሚዎች ስልጠና እየሰጠ ነው

Image
የኢትዮጵያ የምርጫ ህግ በአለም አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ መሰረታዊ የምርጫ መርሆዎችን ያካተተ መሆኑ ተገለፀ፡፡ ይህንን ህግ የምርጫ አስፈፃሚዎች ለ2005 በሚካሄደው የአካባቢ ምርጫ ገለልተኛ ሆነው በብቃት ለመተግበር እንዲችሉ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡ የደባሱ ባይለየኝን ዘገባ ከቀጣዩ ቪዲዮ ይመልከቱ፡፡ ዝርዝር ዜናው እዚህ ተጭነው ይመልከቱ

የሀዋሳ ከነማ ስፖርት ክለብ ታሪክ

Image
አመሠራረት የ የሁለት ጊዜ የኢትዮጲያ ፕርሚየር ሊግ አሸናፊ ሀዋሳ ከነማ ስፖርት ክለብ ከኢትዮጲያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ 273 ኪ . ሜ ዕርቀት እና በ 162.804 ሄክታር ቋዳ ስፋት ላይ በምትገኘው ሀዋሳ ከተማ ይገኛል፡፡ የሀዋሳ ከተማ በ 1953 ዓ . ም የተመሰረተች ሲሆን ከ 1985 ዓ . ም ጀምሮ ደግሞ የደቡብ ክልል ርዕሰ ከተማ በመሆን በማገልገል ላይ ትገኛለች፡፡ የደቡብ ክልል አምብርት በሆነችው ሀዋሳ ከተማ የሚገኘው የሀዋሳ ከነማ ስፖርት ክለብ የተመሰረተው በ 1976 ዓ . ም ነው፡፡ የሀዋሳ ከተማ ባለፈው መንግስት ዘመን በሁለት ከፍተኞች የተከፈለች ከተማ ነበረች፡፡ በሁለቱ ከፍተኞች ስም የተቋቋሙ ሁለት ቡድኖችም ነበሩ፡፡ እነዚህ ቡድኖች ከ 1968-1975 ዓ . ም ከቆዩ በሆላ በ 1976 ዓ . ም ሁለቱ ቡድኖች ተዋህደው ሀዋሳ ከነማ ሊወለድ እንደቻለ ከክለቡ ፅ / ቤት ካገኘነው መረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የሀዋሳ ከነማ ክለብ በሀዋሳ ከተማ የከተማውን ነዋሪ የሚወክል አንድ ቡድን መኖር አለበት በሚል በመዘጋጃ ቤቱ ሃላፊዎች ተነሳሽነትና በነዋሪው ጠያቂነት ሊቋቋም እንደቻለ ታውቋል፡፡ ክለቡ በተጠቀሰው ጊዜ ሲመሰረት ሀዋሳ ሐይቅ በሆላም ቀይ ኮከብ የሚባል ስያሜ እንደነበረው የክለቡ ታሪክ ማህደር ያስረዳል፡፡ የሀዋሳ ከነማ ስፖርት ክለብን ከ 1976 ዓ . ም ጀምሮ በባለቤትነት እያስተዳደረ የሚገኘው የሀዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ነው፡፡ ይሁንና ስፖርት ክለቡ በሂደት ራሱን ችሎ መውጣት አለበት በሚል ህሳቤ ከ 1996 ዓ . ም ጀምሮ አሁን ያለውን አደረጃጀት እንዲይዝ ተደርጓል፡፡ ሙሉ ታሪኩን እዚህ ተጭነው ያንቡ

ሃዋሳ የቱሪስት ከተማ ልትመሰርት ነው

Image
አዲስ አበባ፣ ሀምሌ 24፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) ሃዋሳ ሌላ የቱሪስት ከተማ ለመመስረት በዝግጅት ላይ ትገኛለች። ከተማው የሃዋሳ ሃይቅን ተሻግሮ በሚገኝ ባዶ ቦታ ላይ ነው የሚመሰረተው። በዚህ ከተማ ላይ ለቱሪስት ምቹ የሆኑ ደረጃቸውን የጠበቁ የመዝናኛ ሎጆችና ሪዞርቶች እንደሚገነቡ ነው የከተማዋ ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሴፍ የተናገሩት። የቱሪስት ከተማው ሃዋሳን መርጠው ለመመልከት የሚመጡ የውጭና የሃገር ውስጥ ጉብኝዎችን ቁጥር በተገቢው ሁኔታ ለማስተናገድ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም አመልክተዋል ። የሚመሰረተውን ከተማና ነባሩን ከተማ ለማገናኘት የሚያስችል የትራንስፖርት ስርዓትም እንደሚዘረጋ ተመልክቷል ። እንደ ባልደረባችን  ታደሰ ብዙዓለም ዘገባ የቱሪስት  ከተማዋን ምስረታ  ለመጀመር የሚያስችል ጥናት  ተጠናቆ  ትግበራን  እየተጠባበቀ ይገኛል  ። http://www.fanabc.com/Story.aspx?ID=25131&K=