Posts

በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ በግማሽ የበጀት አመት ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች ከ5 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ገቢ መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ባለስልጣን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ በግማሽ የበጀት አመት ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች ከ5 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ገቢ መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ባለስልጣን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ከበደ መኩሪያ እንደገለፁት ገቢው ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ ብር ብልጫ እንዳለውና የእቅዱ አፈፃፀም 98 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ ለገቢው መገኘት ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ክትትልና የቅርብ ድጋፍ ማድረጋቸው እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤት ጋር በቅንጅት መስራቱ አስተዋጽኦ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡በጽህፈት ቤቱ የገቢ አሰባሰብ የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ፍስሐ በኬ በበኩላቸው ለባለሙያዎች በገቢ አሰባሰብ ስርአት የሚሰጠው የግልፀኝነት፣ የተጠያቂነትና የስነ ምግባር ትምህርት ስራቸውን በታማኝነት እንዲሰሩ አድርጓቸዋል ማለታቸውን የዞኑ ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ዘግቧል ፡፡ ፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/8MegTextN104.html  

በሲዳማ ዞን አርቤጐና ወረዳ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማትን መሰረት ያደረጉ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የወረዳው ግብርና ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በሲዳማ ዞን አርቤጐና ወረዳ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማትን መሰረት ያደረጉ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የወረዳው ግብርና ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሽመልስ ሃጥሶ እንደገለፁት ዘንድሮ በወረዳው ውስጥ በሚገኙ ሁሉም ቀበሌዎች 38 የንኡስ ተፋሰሶችን በመለየት የተለያዩ ተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ስራዎች በመሰራት ላይ ይገኛሉ፡፡ ወረዳው ያለውን ከፍተኛ የውሃ ሀብት ከግምት በማስገባት ጽህፈት ቤቱ በተያዘነው የበጀት አመት 23ዐ ሄክታር መሬት በተለያዩ የውሃ አማራጮች ለማልማት ግብ መጣሉን ገልፀዋል፡፡በእስከ አሁኑ ከ26 ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን በመጠቆም፡፡ አምዛዬ አዳነ ከበንሳ ቅርንጫፍ እንደዘገበው ፡፡ ፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/6MegTextN204.html   

በሲዳማ ዞን ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ህጋዊ ነጋዴዎችን በብዛትና በጥራት ማፍራት መቻሉን የዞኑ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ አስታወቀ :

በሲዳማ ዞን ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ህጋዊ ነጋዴዎችን በብዛትና በጥራት ማፍራት መቻሉን የዞኑ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡መምሪያው ከአንድ ሺህ በላይ ለሚሆኑ ነጋዴዎች የንግድ ፈቃድ ሰጥቶ ወደ ስራ ማስማራቱንም ጨምሮ ገልጿል፡፡ በዞኑ 19 ወረዳዎችና 2 የከተማ አስተዳደሮች 1 ሺህ 4 መቶ 44 የንግድ ፈቃድ ምዝገባ ለማካሄድ ታቅዶ ከዕቅድ በላይ 1 ሺህ 6 መቶ 12 የንግድ ምዝገባ ማከናወን መቻሉን በመምሪያ የንግድ ማስፋፊያ ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ሲኮራ ኤቢሶ ገልፀዋል፡፡በበጀት አመቱ 1ዐ ሺህ 214 የሚሆኑ የንግድ ተቋሟት የምዝገባና የንግደ ፈቃድ አገልግሎት ማግኘታቸውን ገልፀው በዚህም 1 ሚሊዮን 52 ሺህ ብር ገቢ መገኘቱን አስረድተዋል፡፡ሪፖርተራችን ካሳ ጀንቦላ ከበንሳ ቅርንጫፋችን እንደዘገበው ፡፡ ፡፡

በይርጋለም ከተማ በትምህርቱ ዘርፍ የጐልማሶች ትምህርት ውጤት እያስገኘ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ገለፁ :

Image
በይርጋለም ከተማ በትምህርቱ ዘርፍ የጐልማሶች ትምህርት ውጤት እያስገኘ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ገለፁ፡፡የይርጋለም ከተማ ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ተክለስላሴ ዌኬሬ እንዳሉት ሀገሪቱ የተያያዘችውን የትራንስፎርሜሽን እቅድ ለማሣካት የሚቻለው የምክር ቤት አባላት በግንባር ቀደምትነት ተሳታፊ ሲሆኑ ነው ብለዋል፡፡ የከተማው አስተዳደር ከንቲባ አቶ ወንድወሰን ቦልካ በ6 ወራቱ የስራ ክንውን መከላከልን መሰረት ያደረገው የጤና ፖሊሲ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልጿል ፡፡በተለይም በከተማ የጤና ኤክስቴንሽን ረገድ፡፡በትምህርት ዘርፍ የጐልማሶች ትምህርትን ለማጠናከር በተደረገው ጥረትም ውጤታማ ተግባር መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ምክር ቤቱ የ3 ካቢኔ አባላትን ሹመት ያፀደቀ ሲሆን በቀጣይም ለሚሰሩ ተግባራት አቅጣጫ በማስቀመጥ መጠናቀቁን የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል፡፡ ፡፡

በሀዋሣ ከተማ በሳምንቱ ከነበረው የነጭ ጤፍ የገበያ ውሎ በሀላባ ከተማ የ2ዐዐ ብር ቅናሽ መስተዋሉን የክልሉ ግብይትና ህብረት ስራ ቢሮ በላከልን መረጃ አመለከተ ::

Image
በሀዋሣ ከተማ በሳምንቱ ከነበረው የነጭ ጤፍ የገበያ ውሎ በሀላባ ከተማ የ2ዐዐ ብር ቅናሽ መስተዋሉን የክልሉ ግብይትና ህብረት ስራ ቢሮ በላከልን መረጃ አመለከተ፡፡በሀላባ ከተማ 1 ኪሎ በርበሬ 42.5ዐ ሳንቲም ዋጋ ሲሸጥ በሀዋሣ ከተማ የ14 ብር ጭማሪ አሳይቷል ፡፡በዛሬው የገበያ ውሎ ዳሰሳችን በሳምንቱ የሀዋሣ፣ ሆሣዕናና ሀላባ ከተሞች ገበያ ውሎን እናስቃኛችሁአለን፡፡ በሳምንቱ ከነበረው የገበያ ውሎ ነጭ ጤፍ በሐዋሣ ከተማ ኩነታሉን 1 ሺህ 37ዐ ብር በችርቻሮ የተሸጠ ሲሆን የ7ዐ ብር ቅናሽ በማሳየት በሆሣዕና ከተማ 1ሺህ 3ዐዐ ብር በሀላባ ከተማ 2ዐዐ ብር ቅናሽ በማሳየት ኩንታሉ በችርቻሮ 1ሺህ 17ዐ ብር ሲሸጥ ሰንብቷል፡፡ከብርዕ ሰብል ወደ አገዳ ሰብል ስናመራ በቆሎ በሀላባ ከተማ ኩንታሉን በችርቻሮ 43ዐ ብር ተሽጧል፡፡ በሆሣዕና የ1ዐዐ ብር ጭማሪ በማሳየት 53ዐ ብር እንደዚሁም በሐዋሣ ከተማ 54ዐ ኩንታል በችርቻሮ ንግድ ተሽጧል፡፡ ወደ ጥራጥሬ እህል የገበያ ውሎ ስንሸጋገር ደግሞ አንድ ኩንታል አተር በሐዋሣ ከተማ በችርቻሮ 1ሺህ 62ዐ ብር ሲያወጣ በሆሣዕና ከተማ 12ዐ ብር ቅናሽ በማየት የ1ሺህ 5ዐዐ ዋጋ አውጥቷል፡፡ በሀላባ ገበያ በመሸጥ ከሆሣዕና ገበያ 14ዐ ጭማሪ ተስተውሏል፡፡የአትክልትና የስራስር ተክሎች ሳምንታዊ የገበያ ውሎን ስንመለከት አንድ ኪሎ ቲማቲም በሆሣዕና ከተማ 12 ብር ሲሸጥ የሰነበተ ሲሆን በሀላባ ከተማ የ3.5ዐ ሳንቲም በሀዋሣ ከተማ ደግሞ የ4 ብር ቅናሽ በማሳየት ተሽጧል፡፡ ቀይ ሽንኩር 1 ኪሎ ግራም በሐዋሳ ከተማ በችርቻሮ ተሽጧል፡፡ በሆሣዕናና በሀላባ ከተሞች ደግሞ የ9 ብር ዋጋ አውጥቷል፡፡ ነጭ ሽንኩርት በሆሣዕና ከተማ 1 ኪሎ 5ዐ ብር በሀላባ 46 ብር እንደዚሁም የሀዋሣ ከተማ የ14 ብር ቅናሽ በማሳት በ3