Posts

Addis to Mombassa Road connect the coffee growing areas of southern Ethiopia with Hawassa Town, the capital of Southern Regional State, the head of the authority claimed.

The Ethiopian Roads Authority (ERA) awarded two parts of the construction of the second phase of the Mombassa-Nairobi-Addis Abeba Road corridor to an Egyptian based construction company, at a cost of around 740.7 million Br, on Wednesday, March 29, 2011. The ERA also signed comprehensive road project agreements worth a total of 2.6 billion Br with four local companies for the construction of 242.8km of roads in Tigray and Amhara regional states. The Hagere Mariam-Mega asphalt road rehabilitation and 94.5km Hagere Mariam-Yabelo concrete pavement construction projects, both in Oromia Regional State, were awarded to Arab Contractors (Osman Ahmed Osman & Co). Both form part of the Mombassa-Nairobi-Addis Abeba corridor, an important part of the Trans-African Highway between Cairo and Cape Town. "This is the first time an Egyptian company has signed an agreement for road construction in Ethiopia," said Zayed Woldegebriel, director general of the ERA, at the signing of the co

አዲስአበባ፣መጋቢት11፣2003 ትናንት ምሽት በይርጋለም ከተማና በሲዳማ ዞን ወንሾወረዳ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ።

በይርጋለም ከተማ ልዩ ስሙ አቦሶ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ትናንት ምሽት 5 ሰአት ከ 8 ደቂቃ ላይ የከተሰተው። የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር እስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበበት መሆኑን በአዲስ አበባዩኒቨርስቲ የጂኦፊዚክስ ስፔስ ሳይንስ አስትሮኖሚ ኢኒስቲትዩት ተመራማሪ ዶክተር ኤልያስ  ሌዊ ተናግረዋል። በሌላ በኩል በሲዳማ ዞን ወንሾ ወረዳም ትናንት ምሽቱን ተመሳሳይ የመሬት መንቅጥቀጥ አደጋደርሷል። የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘውዴ ገቢባ ለኢዜአ እንደተናገሩት በወረዳው በሚገኙ 17 ቀበሌዎችላለፉት 10 ቀናት በተወሰነ የሰዓት ልዩነት በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት ቆይቷል፡፡ ትናንት ከምሽቱ 5 ሰዓት ከ 10 ደቂቃ ላይ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የወረዳውአስተዳደር ጽህፈት ቤትን ጨምሮ ከ 100 የሚበልጡ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ፈርሰዋል። ጉዳትየደረሳበችው ሁለት ግለሰቦችም በይርጋለምና ቦካሶ ጤና ጣቢያ ህክምና እያገኙ ሲሆን 10 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ግምት ያለውንብረትም ወድሟል።

Unusual moderate, but dangerous earthquake near Yirgalem, Ethiopia

Image
Today March 19 ,2011 at 11:09 PM earthquake happened at yirgalem its real earth quake (shake) it didn’t cause any disaster as far as I have seen it, but everybody felt it for 4 seconds. It was the longest quake I have witnessed in my life. Everything in my house was  shaking. Some books were dropped to the floor. Electric power also gone for 10 minutes .and I fell the shake at 7:57 am for 1 second again . UPDATE 20/03-01:09 UTC :  The shaking lasted for about 4 seconds. Original article

በዓይነቱና በይዘቱ ለየት ያለ ዘመናዊ ሁለገብ ስታዲየም በ700 ሚሊዮን ብር ወጪ በሐዋሳ ልገነባ ነው።

በዓይነቱና በይዘቱ ለየት ያለውን ዘመናዊ የሐዋሳ ሁለገብ ስታዲየም ግንባታ ለማስጀመር የተካሄደው የማስታወቂያ ፕሮግራም ሳምንታትን አስቆጥሯል፡፡ስራውን በተግባር ለመጀመር አንድ ነገር ቀርቶ ነበር፡፡ የሁለገብ ስታዲየሙን ግንባታ ገቢ አሰባሳቢና አስተዳደር ምክር ቤትን ማቋቋም፡፡ እሱም ባለፈው እሁድ በሐዋሳ ሃይሌ ሪዞልት እውን ሆኗል፡፡   ምክር ቤቱ የተቋቋመው የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የሐዋሳ ከተማ፣ የዞንና የልዩ ወረዳ አስተዳደሮች፣ ባለሐብቶች እና የሃይማኖት አባቶች በተገኙበት ነበር፡፡ የምክር ቤቱን መቋቋም ተከትሎ ግንባታውን ለማስጀመር የገቢ ማሰባሰብ ሂደቱ ምን ይሁን በሚለው ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ከተደረገ በኋላ ሐዋሳ ስታዲየም ቴሌቶን 2003 በሚል ስያሜ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የስራውን በይፋ መጀመር አብስረዋል፡፡ ለሁለገብ ስታዲየሙ ግንባታ እውን መሆን የክልሉ ህዝብ ፣ ከአገር ውስጥ እና ውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መረባረብ እንደሚጠበቅባቸው ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ 28 ሄክታር መሬት ላይ ያርፋል ተብሎ የሚጠበቀው ሰታዲየሙ አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሲሆን እስከ 45 ሺህ መቀመጫ ያለው የእግር ኳስ ሜዳ፣ ዘመናዊ የአትሌቲክስ መወዳደሪያ እና ሌሎች 16 ዓይነት የስፖርት ውድድሮችን ማስተናገድ የሚችል ሜዳ ያካትታል፡፡ ለግንባታው እስከ 700 ሚሊዮን ብር ሊጠይቅ ይችላልም ተብሏል፡፡ ይህ የከልሉ ህዝብ ታሪክ የሆነው ስታዲየም ግንባታ የ 56 ቱም ብሄረሰቦች መገለጫ ሙዚየም በመሆኑ የዞን እና ወረዳ አስተዳደሮችም ህብረተሰቡን በማሳተፍ የበኩላቸውን ድጋፍ ለመወጣት በቁርጠኝነት ለመስራት ዘግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡

የሴቶች ማሕበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት እየጐለበተ መምጣቱን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች መምሪያ ገለፀ፡፡

መምሪያው የማርች 8 በዓልን ከከተማው የተውጣጡ አመራሮች፣የየክፍለ ከተማው ተወካዮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በተለያዩ ዝግጅቶች አክብሮ ውሏል፡፡ ሴቶች ሕገመንግስቱ ባረጋገጠላቸው መብቶችና ጥበቃወች በመጠቀም ረገድ ከወንዶች እኩል መብት እንዳላቸው እንዲሁም ከተለያዩ ፆታን መሠረት ካደረጉ ጐጂ ልማዳዊ ድርጊቶች የመጠበቅና አገልግሎት የማግኘት መብታቸው የተጠበቀ መሆኑ በግልፅ ተደንግጓል፡፡ በዓሉ የሀገራችን ሴቶች በሕገ መንግስቱ የተረጋገጠላቸው መብቶች ለማስከበር የትግል አንድነታቸውን የሚያጠናክሩበት የተጀመረውን የሠላምና የዴሞክራሲያዊ ጐዞ እንዳይቀለበስ ለማድረግ እንዲሁም በኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊና ማሕበራዊ ዘርፎች በንቃት ተሳትፈው እና ተጠቃሚ ለመሆን ትግላቸውን የሚያጠናክሩበት ነው፡፡ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ - ጉባኤ አቶ ደምሴ ዶንጊሶ በዓሉን በንግግር ሲከፍቱ እንዳሉት በሀገሪቱ በክልሉና ሆነ በከተማው ከተመዘገቡ ፈጣን የኢክኖሚ ዕድገት የሴቶችን ተሳተፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ባለፉት 20 ዓመታት በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ሕገ መንግስቱ መሠረት በማድረግም በክልሉ የቤተሰብ ሕግ ተሻሽሎ መውጣቱ ሴቶተ ቤተሰብን በመገንባት ረገድ እኩል መብትና ኃላፊነት እንዲሃራቸው ማድረጉ ይጠቀሳል ብለዋል፡፡ የከተማው ሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሪት ሥምረት ግርማ በበኩላቸው በዓሉ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ከማጐልበቱ በተጨማሪ ሴቶች በድንበር፣በኃይማኖት፣በቀለም፣በቋንቋ እንዲሁም በባሕል ሳይለያዩ የሚደርሱባቸውን ጭቆናና መማሎ የሚያወግዙበት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በዕለቱም ሥርዓተ ፆታና ልማት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ያለው ፋይዳ እንዲሁም የሴቶች የተደራጀ ተሳትፎና ንቅናቄ ለዕቅዱ ስኬት ያለው