የሲዳማ ዞን መንግስት ከዞኑ ውጪ ነዋሪ በሆኑ የሲዳማ ብሔር ተወላጆች ላይ እየተፈጸመ ያለውን ኢሰብኣዊ ድርጊት ማስቆም ኣልቻለም፤ በኦሮሚያ ክልል በባሌ ሮቤ ዞን የሀንጌቱ ወረዳ ኣስተዳደር የሲዳማ ብሔር ተወላጆችን እያፈናቀለ ነው
በቃጠሎ ከወደሙ ቤቶች መካከል በቃጠሎ ከወደሙ ቤቶች መካከል በቃጠሎ ከወደሙ ቤቶች መካከል 4 6 ቤቶች ከእነ ንብረታቸው በቃጠሎ ወድሟል፤ 400 የሲዳማ ብሄር ተወላጆች ከፍተኛ ድብደባ ተፈጽሞባቸው ከኣከባቢው እንዲሰደዱ በመደረጋቸው ከ 2 ወራት በላይ በጫካና በዱር እየተንገላቱ ነው በኦሮሚያ ክልል በባሌ ሮቤ ዞን በሀንጌቱ ወረዳ ለኣመታት ከኣከባቢው ህዝብ ጋር ተጋብቶ ና ተዋልዶ በሰላም የኖ ሩት የሲዳማ ብሔር ተወላጆች በወረዳው ኣስተዳደር ቤት ንብረ ታቸውን ተቀምተው ከኣከባቢው እንድለቁ በመደረግ ላይ ናቸው። ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና ከሃዋሳ የላከልክ ዘጋባ እንደሚያመለክተው ከሆነ፤ በወረዳው ኣስተዳዳር የተመራው የጸጥታ ኃይል በኣንድ ቀን ብቻ 46 ቤቶች ከእነ ንብረታቸው በማቃጠል፣በ 400 ሰዎች ላይ ከፍተኛ ድብደባ በመፈጸም ለዘመናት ከኖሩበት አካባቢ እንድሰደዱ እና ከ 2 ወራት በላይ በጫካና በዱር እንድገላቱ ኣድርጓል። ከ 400 በላይ በደል የደረሰባቸው የሲዳማ ተወላጆች በተወካዮቻቸው የደረሰባቸውን ኢሰብኣዊ ድርጊት በመቃዎም ብሎም በደ ሉ እንዲቆምና በደል የፈፀሙ አካላት በህግ እንዲጠየቁ ተፈናቃዮች ለፌዴራል ጉዳይ ሚንስቴር አቤቱታ ቢያቀርቡም አቤቱታውን የተቀበለ አካል ጉዳዩ እንዲጣራ ለኦሮሚያ ክልል መንግስት በስልክ ትዕዛዝ ሠትተናልና ሄዳችው የሚሰጣችሁን መልስ ጠብቁ የምል ምላሽ መሰጠቱ ታውቋል ፡፡ ሆኖም እስከ ዛሬ ድረሰ ምንም መፍትሄ ሳይሰጥ ተጨማሪ ነዋሪዎች ላይ ንብረት የማውደምና የማፈናቀል እርምጃ ተጠናክሮ ቀ ጥሏል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የተፈናቃዮችን አቤቱታ ተቀብሎ ለባሌ ዞን አስተዳደር ጽ / ቤትና ለሀረና ቡሉቅ ወረዳ አስተ