Posts

በሲዳማ ዞን ከ186ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት የበጎ ፈቃድ ፕሮግራም በይፋ ተጀመረ፡፡

Image
photo http://www.flickr.com/photos/espsol/sets/72157632677473483/ አዋሳ ሐምሌ 11/2005 በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞን ከ186ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራም ትናንት ተጀመረ ። የወጣቶችን የስራ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት እንዲጠናከር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የክልሉ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ጥሪ አቀረቡ፡፡ የፕሮግራሙ መጀመር ምክንያት በማድረግ በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ ትናንት በተዘጋጀው መድረክ ላይ የዞኑ ሴቶች፣ ወጣቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ኃለፊ ውይዜሮ ሻሎ ሮርሳ እንደገለጹት የዞኑ ወጣቶች ባለፉት አራት ዓመታት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደራጀ መንገድ በመሰማራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባሮችን ሲያከናዉኑ ቆይተዋል ። የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን ወጣቶቹ ጉልበታቸውን፣ እውቀታቸውን ለአካባቢው ልማት በማዋል መልካም ተግባሮችን ከማከናወናቸዉም ሌላ ከማህበረሰቡ የተለያዩ እሴቶችን የቀስሙበት እንደነበር አስታዉቀዋል ። በዘንድሮም ክረምት ከዞኑ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ከወጣት አደረጃጀቶች ጋር በመተባበር እራሳቸውንና ህብረተሰቡን ጠቅመው የዞኑን ልማት በሚያፋጥኑ የልማት ተግባሮች ለመሰማራት እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ወይዜሮ ሻሎ አብራርቷል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢህዴን/ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አክልሉ አዱሎ በበኩላቸው የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ በከተማው ከተጀመረ ወዲህ ወጣቶች ለልማት ያላቸዉ ተነሳሽነትና ፍላጎት እየጨመረ መጥቷል ብለዋል፡፡ ወጣቶቹ በቆይታቸዉ የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት ፣ የአካባቢ ጥበቃ፣ የጤና፣ የአካባቢ ፅዳትና ውበት፣ የትራፊክ ደህንነት፣ አረጋውያንና

ኣገሬ ሰላም እኣኣ በ1963 እስከ 1967 ከ60 ኣመት በፊት በፎቶ

Image
ተጨማሪ ፎቶ ለማየት እዚህ ላይ ይጫኑ

Hawassa University graduation ceremony Main Campus(Photos )

Image
Hawassa University graduation ceremony Main Campus take a look at photos

በሀዋሳ ከተማ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ ተሰጠ

Image
አዋሳ ሐምሌ 10/2005 በሀዋሳ ከተማ በተጠናቀቀው በጀት አመት ከ523 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 56 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ ለመግባት እየተዘጋጁ መሆናቸውን የከተማው ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ ገለጸ፡፡ በከተማው የዘንድሮን ሳይጨምር 5 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያላቸው ሌሎች ባለሀብቶች በፈጠሯቸው የስራ እድሎች ከ28ሺህ 600 ለሚበልጡ ዜጎች ተጠቃሚ ማድረጋቸውም ተገልጿል፡፡ በመምሪያው የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠት ፐርፎርመርና የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ወግደረስ ወንድሙ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በተጠናቀቀው የበጀት አመት ከ523 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል በማስመዝገብ ፍቃድ የወሰዱት 56 ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ፣ በኮንስትራከሽን ፣በሆቴልና ሌሎች ማህበራዊ አገልገሎቶች ለመሰማራት ነው፡፡ ባለሀብቶቹ በግላቸው ባላቸውና በጊዜዊነት በተሰጣቸው ቦታዎች በአሁኑ ወቅት ወደ ስራ ለመግባት በዝግጅት ላይ መሆናቸውና ስራ የጀመሩ እንዳሉ አመልክተው በሙሉ አቅማቸው ሲንቀሳቀሱ 2ሺህ ሰዎች የስራ እድል ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ለኢንቨስትመንት ልማት የሚውል 420 ሄክታር የሚጠጋ መሬት ዘንድሮ በጥናት ተለይቶ ለአልሚ ባለሀብቶች መዘጋጀቱንና ከዚሀም ውስጥ 270 ሄክታር በሀገር አቅፍ ደረጃ በማዕከላዊ መንግስት ለአንዱስትሪ ልማት የሚፈለግ ነው ብለዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለኢንዱስትሪ ልማት ከተመረጡ አምስት ከተሞች መካከል ሀዋሳ አንዷ በመሆኗ ማዕከላዊ መንግስት ከውጪና ከሀገር ውስጥ ለሚጋብዛቸው አልሚ ባለሃብቶች እንዲውል ያዘጋጁት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ቀሪው 150 ሄክታር መሬት በኢንዱስትሪ፣ በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣በሪል ስቴትና በአገልግሎት ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብ

ሃዋሳን ጨምሮ የከተሞች ማስፋፍያ እና የኢኮኖሚ እድገት መርሀ ግብር ተግባራዊ ሊሆን ነው

Image
የከተሞች የተቀናጀ ማስፋፍያ እና የልማት መርሀ ግብርን ተግባራዊ ማድረግ በከተሞች አያደገ ለመጣው የመሬት አቅርቦት ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ እንደሚሰጥ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የከተሞች ማስፋፍያ እና አካባቢ ልማት መርሀ ግብር ማስጀመሪያ ወርክሾፕ እየተካሄደ ነው፡፡ የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር አቶ ሞክርያ ሀይሌ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በከተሞች መሰረተ ልማት፣ እድገት እና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትኩረት ያደረገ ስትራቴጂ ተግባራዊ ተደርጎ በከተሞቹ የማስፈፀም አቅምና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ውጤት የተገኘ ቢሆንም የተቀናጀ የከተሞች ማስፋፋትና የልማት ፕሮግራምን ውጤታማ ከማድረግ አንፃር ግን ብዙ መስራት ይጠበቃል ብለዋል፡፡ አሁን በኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ ድጋፍ አድራጊነት በሙከራ ደረጃ በአራት ከተሞች ላይ ተግባራዊ የሚደረገው የከተሞች ማስፋፊያ እና አከባቢ ልማት መርሀ ግብር ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚያግዝም ጠቁመዋል፡፡ መርሀ ግብሩ በፈጣን የከተሞች መስፋፋት እና የኢኮኖሚ እድገት ሳቢያ እያደገ ለመጣው የቤቶችና ኢንዱስትሪ ግንባታዎች የመሬት አቅርቦት እንዲኖር ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር ባለፈ የከተሞችን ገቢ በማሳደግ ረገድም ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሏል፡፡ መርሀ ግብሩ በሙከራ ደረጃ በአዳማ፣ ሀዋሳ፣ ባሀርዳር እና መቀሌ ከተሞች ላይ ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን በመጪው ጥር ወር ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ፅሕፈት ቤት ዘግቧል፡፡ http://www.ertagov.com