Posts

ተቃዋሚዎች ከኢህአዴግ ጋር ድርድር እንፈልጋለን አሉ

Image
በመጪው ግንቦት ወር በሚካሄደው የአካባቢና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ላይ ከመወያየታችን በፊት በምርጫው ዲሞክራሲያዊነትና ነፃ መሆን ላይ ልንወያይ ይገባል በሚል ለምርጫ ቦርድ በደብዳቤ ጥያቄ ያቀረቡ 34 ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ የምርጫ ምልክት ውሰዱ መባሉን ተቃወሙ፡፡ በምርጫ ቦርዱ ላይ እምነት ስለሌለን ከኢህአዴግ ጋር ያለቅድመ ሁኔታ ድርድር እንፈልጋለን ብለዋል - ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ፡፡የኢህአዴግ ጽ/ቤት ቢሮ ኃላፊና በጠ/ሚኒስትሩ የህዝብ አደረጃጀት አማካሪ አቶ ሬድዋን ሁሴን በበኩላቸው፤ የምርጫ ስነምግባር ደንቡን ካልፈረሙ ፓርቲዎች ጋር አንደራደርም ብለዋል፡፡  ፓርቲዎች የምርጫ ምልክታቸውን እስከፊታችን ሰኞ እንዲወስዱ ምርጫ ቦርድ ያስታወቀ ሲሆን ተቃዋሚዎች በበኩላቸው፤ ለቦርዱ ደብዳቤ በማስገባት ምላሽ እየጠበቁ ባሉበት ሰዓት የምርጫ ምልክት ውሰዱ መባላቸው አግባብ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡ ተቃዋሚዎች ላቀረቡት ጥያቄ ምርጫ ቦርድ “ምላሽ የሚሰጠው ተገቢ ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ ነው” ሲል ለአዲስ አድማስ መግለፁ ይታወሳል፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ በቦርዱ ላይ እምነት እንደሌላቸው በመግለፅ፡- ከኢህአዴግ ጋር ውይይት እንደሚፈልጉና ከዛ በፊት የምርጫ ምልክት እንደማይወስዱ አስታውቀዋል፡፡ የመድረክ የስራ አስፈፃሚ አባልና የ34ቱ ፓርቲዎች ጊዜያዊ ኮሚቴ ዋና ሰብሳቢ አቶ አስራት ጣሴ ለአዲስ አድማስ ሲያስረዱ፤ “ከዚህ ቀደም የተደረጉ ምርጫዎች ችግር የነበረባቸው በመሆናቸው ከጊዜ ሰሌዳው በፊት በምርጫው ፍትሃዊነትና ዲሞክራሲያዊነት ላይ ውይይት እንዲደረግ ፒትሽን ተፈራርመን ለቦርዱ አስገብተን፣ ለሱ ምላሽ ሳይሰጥ ምልክት ውሰዱ መባሉ ተገቢ አይደለም” ብለዋል የምርጫ ቦርዱ ተአማኒነትና ተቀባይነት ጥያቄ ውስጥ ነው ያሉት አቶ አስራት ጣሴ፤ ከኢህአዴግ

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ 35 ኣምስተኛውን የምስረታ በዓል በደማቅ ሁኔታ ኣከበረ፤ ኣዳዲስ የድርጅት ኣመራር መርጧል

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ 35 ኣምስተኛውን የምስረታ በዓል በደማቅ ሁኔታ ኣከበረ፤ ኣዳዲስ የድርጅት ኣመራር መርጧል በዛሬው እለት በሃዋሳ ከተማ በዳግም ጂሚናዥዬም በተካሄደው የምስረታ  ሰነስርኣት ላይ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ  35 ኣመት የምስረታ በኣል በተለያዩ  ዝግጅቶች ኣክብሯል። በርካታ የድርጅቱ ደጋፊዎች በተገኙበት በተካሄደው በዚህ ስነስርኣት ላይ ለሲዳማ ህዝብ ነጻነት ለተሰው ሰማዕታት የህልና ጸሎት የተደረገ  ሲሆን ድርጅቱን በቀጣይነት የምመሩ ኣመራሮች ተመርጠዋል። በኣጠቃላይ 15 ኣባላት ያሉት በኣብዛኛው ወጣቶችን የሆነና የዩኒቨርሲቲ ተማርዎችን ያቀፈ የድርጅት ኣመራር የተመረጠ ሲሆን ኣንጋፋ የሲዳማ ታጋዮችን በኣመራርነት ተካተዋል። በኣመራርነት ከተመረጡት መካከል ካላ ዋቃዮ፤ ዶክተር ኣለማዬሁ፤ እና ካላ ካሳ ኣዲሶ  ይገኙበታል። ክቡራን ኣንባቢያን  ዝርዝር ዜናውን እንደደረሰን እናቀርባለን

በሲዳማ ዞን ሎካ አባያ ወረዳ በየደረጃው ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሠራጨት ግብ ጥሎ እየሠራ መሆኑን የወረዳው ኦሞ ማክሮ ፋይናንስ ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በሲዳማ ዞን ሎካ አባያ ወረዳ በየደረጃው ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሠራጨት ግብ ጥሎ እየሠራ መሆኑን የወረዳው ኦሞ ማክሮ ፋይናንስ ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ሀይለኢየሱስ እንደገለፁት መንግስት የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል በነደፈው ስትራቴጂ መሠረት በተያዘው በጀት ዓመት 1ዐ ሚሊዮን ብር ብድር ለማሰራጨት እና 18 ሚሊዮን ብር ከቁጠባ ለመሰብሰብ አቅዶ እየሰራ ነው፡፡ ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ከንግድና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር ከተለያዩ ዩንቨርስቲዎችና ኮሌጆ  ለተመረቁ  ተማሪዎችን ከ5 መቶ ሺህ ብር በላይ የብድር አገልግሎት ለመስጠት ማቀዱን ገልፀዋል፡፡ በተያዘው እሩብ በጀት ዓመት 3 ሚሊዮን 6 መቶ ሺህ ብር ብድር ማሰራጨቱንና መቶ ሺህ ብር ቁጠባ መሰብሰብ መቻሉን ጠቁመው 6 ሺህ 8 መቶ የሚሆኑ የህብረተሰቡ ክፍሎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል ሲል ሪፖርተር አካሉ ጥላሁን ከበንሳ ቅርንጫፍ ጣቢያ ዘግቧል፡፡

Human Rights Violations in Sidama, Southern Ethiopia

Appeal to:- Mr. Ban Ki -Moon, United Nation’s Secretary General, United Nations, 760 United Nations Plaza Manhattan, NY 10017, USA Mr. José Manuel Barroso President of the European Commission 1049 Brussels, Belgium Mrs. Inkosazana Dlamini Zuma, African Union’s Secretary General P.O. Box 3243 Roosvelt Street (Old Airport Area) W21K19 Addis Ababa, Ethiopia Secretary Hillary Rodham Clinton The US Department of State 2201 C Street Northwest Washington, DC, USA 20 November 2012 Subject: - Human Rights Violations in Sidama, Southern Ethiopia The Sidama people live in Southern Ethiopia. According to the Ethiopian Government’s official statistics, the current population of Sidama is 3.4 million (independent estimates suggest that the current total population is above 5 million). The Sidama nation had a long history, vibrant culture and democratic systems of governance based on traditional Kingships and various democratically elected traditional councils of elders. This traditional system of go

የህብረተሰብ ጤና ልማት ሰራዊትን ለመገንባት 63 ሺህ በላይ ሞዴል ቤተሰቦች ማፍራቱን የሀዋሣ ከተማ ጤና መምሪያ ገለፀ፡፡መምሪያው የ2ዐዐ5ሩብዓመትእቅድክንውንገምግሟል፡፡

Image
የእቅድ ክንውን ሪፖርት በቀረበበት ወቀት የመምሪያው ኃላፊ አቶ ደሰታ ዶጊሶ አንደተናገሩት በሩብ አመቱ የእናቶችንና የህፃናትን ሞት ለመቀነስ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ከከተማዋ ፈጣን እድገት ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ የጤናና የማህበራዊ ችግሮች በመፈታት ነዋሪውን ጤናማ፣ አምራችና የበለፀገ ለማድረግ የጤና ልማት ሰራዊት ግንባታ ተግባራዊ መሆን መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡ የህብረተሰብ ጤና ልማት ሰራዊትን ከመገንባት አንፃርም ከ63 ሺህ 993 ሞዴል ቤተሰቦች ማፍራቱን ተናግረዋል፡፡ በሪፖርቱ እንደቀረበው የሳንባ ነቀርሳ በሽታን መከላከያ ክትባት ለ2 ሺህ 678 ህፃናት ለመስጠት ታቅዶ 2 ሺህ 971 የተከናወነ ሲሆን ባለፈው ሩብ አመት አብዛኛዎቹ አፈፃፀሞች ከእቅዱ 9ዐ በመቶ እና ከዚያ በላይ ተግባራዊ መሆናቸው በሪፖርቱ ቀርቧል፡፡ ከመንጋጋ ቆልፍ በሽታ የተጠበቀ ህፃናት እንዲወለዱ ከማድረግ አንፃርም በሩብ አመቱ 2 ሺህ 678 ህፃናት አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ከእቅድ በላይ መከናወኑንም ተጠቁሟል፡፡ በመቀጠልም በበጀት ዓመቱ የጤና ሴክተር ትኩረት የሚያደርገው የጤና ተቋማት በማስፋፋትና በግብዓት በሟሟላት የጤና አገልግሎቶች ጥረት ማሻሻል የእናቶችና የህፃናት ሞትን በመቀነስና ዋና ዋና ተላላፊ በሽታዎችና መከላከልና መቆጣጠር ላይ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች አማካኝነት 124 እናቶች የወሊድ አገልግሎት ለመስጠት እቅድ ተይዞ ለ49 እናቶች ብቻ አገልግሎት የተሰጠ ሲሆን በቀጣይም በተሻለ ሁኔታ ለመስራት ጥረት እንደሚያደርግ ተገልጿል፡፡ በምክክር መድረኩም የሀዋሣ ክፍለ ከተሞች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት የጤና ባለሙያዎች እና ሌሎች አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡http://www.smm.gov.et/_Text/1