Posts

ደኢህዴን መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው

Image
አዲስ አበባ (ኢዜአ)፡- የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢህዴን/ ማዕከላዊ ኮሚቴ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዘመንን የሁለተኛ ዓመት መደበኛ አፈጻጸምና የታላቁ መሪን የመለስ ዜናዊን ራዕይ ለማሳካት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በዝርዝር ገመገመ፡፡ ለታላቁ መሪ ጓድ መለስ ዜናዊ የህሊና ጸሎት በማድረግ ማዕከላዊ ኮሚቴው ትናንት በጀመረው መደበኛ ስብሰባ ታላቁ መሪ ባወጡት ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች በሚፈጸምበት ዝርዝር ሁኔታ ላይ ተዘጋጅተው በቀረቡ ሰነዶች ላይ በመወያየት አቋም ወስዷል። ድርጅቱ በላከው መግለጫ እንዳብራራው፤ በየደረጃው የሚገኙትን ድርጅታዊ፣ መንግሥታዊና ህዝባዊ አመራሮችንና አደረጃጀቶችን ተቋማዊ በማድረግ የህዳሴውን ጉዞ ለማሳካት በቀረበ ሰነድ ላይ በመወያየት የአፈጻጸም ሰልቶች ተቀይሶ በፍጥነት ተግባራዊ እንዲሆን ውሳኔ አሳልፏል። በገጠር ሥራዎች ረገድ ባለፈው ዓመት በአካባቢ ልማት ጥበቃ የነበረው የህዝብ አደረጃጀት ተሳትፎ ከቀዳሚዎቹ ዓመታት የተሻለ አፈጻጸም የታየበት ሲሆን፤ ወደ በልግ መኸር የግል ማሳ ሥራዎች በመሸጋገር ረገድም በአንዳንድ አካባቢዎች መልካም ውጤቶች መመዝገባቸውን የማዕከላዊ ኮሚቴ አረጋግጧል። ምርትንና ምርታማነትን ለማሳደግ ሁሉንም የቴክኖሎጂ ግብዓቶች እጅ በእጅ በመግዛት ጥመርታውን ጠብቆ ጥቅም ላይ በማዋል ረገድ የነበሩ ክፍተቶችን በዝርዝር መመልከታቸውን መግለጫው ጠቁሟል። በከተሞች በሥራ ፈጠራ፣በቤቶች ልማት፣በማህበራዊና በመሰረተ ልማት ዝርጋታ የታየው ለውጥ የተሻለ ሲሆን፤ በየደረጃው የሚቀርቡ ጥያቄዎችን በአግባቡ ተገንዝቦ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ረገድ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ጉድለቶችን በቀጣይ ሊታረሙ እንደሚገባ የማዕከላዊ ኮሚቴው አስገንዝቧል፡፡  የኮሚቴው መደበኛ ስብሰባ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ45ኛ ዳኞችን ሹመት አፀደቀ

Image
አዲስ አበባ፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ያቀረቡትን የ45 ዳኞች ሹመት አፀደቀ። የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስን ዓመታዊ የመክፈቻ ንግግር ሞሽን ላይ በሚቀጥለው ሳምንት ለመነጋገር ወሰነ። ምክር ቤቱ ትናንት ባካሄደው ሦስተኛ የሥራ ዘመን በአንደኛ መደበኛ ስብሰባው ሹመታቸውን ካፀደቀላቸው 45 ዳኞች መካከል አምስቱ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ዘጠኙ ለከፍተኛ ፍርድ ቤት እንዲሁም 31ዱ ለመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በእጩነት የቀረቡ ናቸው። በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ስለቀረቡት እጩ ዳኞች ለምክር ቤቱ በዝርዝር ያስረዱት የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መለስ ጥላሁን፤ ዳኞቹ የሕግ ምሩቃን፣ በሙያው በቂ ልምድ ያላቸው፣ ለሕገ መንግሥቱ ታማኝ፣ በሥነ ምግባራቸው መልካም ስም ያተረፉና በዳኝነት ሙያ ለመስራት ፍላጎት ያላቸው መሆናቸውን ለምክር ቤቱ አስረድተዋል። እጩ ዳኞቹ የተመረጡበትን መስፈርት በተመለከተ አንድ የምክር ቤቱ አባል የእጩዎቹ ምርጫ የብሔር ስብጥርን በተለይም የታዳጊ ክልሎችን ግምት ውስጥ ያስገባ እንዳልሆነ አስተያየት ሰጥተዋል። ሌላኛው የምክር ቤቱ አባል ደግሞ የዳኞቹ ሹመት የተረሱ ብሔረሰቦችን ሲያካትት በታሪክ የመጀመሪያው እንደሆነ በመግለጽ ሹመታቸው ከፀደቀላቸው ዳኞች መካከል የአርጎባ ብሔረሰብ አባል በመካተታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። የተቃዋሚ ፓርቲ አባል የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ በበኩላቸው፤ ከዚህ ቀደም በነበረው የዳኞች ሹመት ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች ብቻ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ግን ከግል የትምህርት ተቋማት የተመረቁትን ጨምሮ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተካተቱበት መሆናቸውን በማድነቅ ይህ ሊለመድ እንደሚገባ አስተያየት ሰ

የተባበሩት የሲዳማ ፓርቲዎች ለቅንጅት ነጻነት እና ለፍትህ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጠ፤ ኣዲሱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኣቶ ኃይለማሪያም ደሳሌኝ የሲዳማን ህዝብ ክልል የመሆን ህገ መንግስታዊ መብት እንዲያከብሩ ጠየቀ

Image
ፓርቲው ለወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ በላከው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳመለከተው የኢትዮጵያ መንግስት የሲዳማን ህዝብ በክልል ደረጃ ራስን በራስ የማስተዳደ መብት እንዲያከብር ጠይቀዋል። የጋዜጣዊ መግለጫው ሙሉ ቃል እንደምከተለው ቀርቧል፦ The New Ethiopian Prime Minster ‘Hailemariam Desalegn’ Must Respect Sidama people’s Constitutional Rights to Regional Self Administration!! Press Release By United Sidama Parties for Freedom and Justice (USPFJ), October 11, 2012 The Sidama nation endured various forms and shapes of injustices imposed on them by the successive Ethiopian rulers including the current TPLF/EPRDF’s regime. The injustices the Sidama nation is exposed to involve an economic and political marginalization, socio-cultural subjugation and gross violations of their fundamental rights. Even though the Sidama nation owns one of the richest regions in the country, its people are subjected to a persistent government induced poverty that had chronologically deepened from time to time. Sidama’s development institutions are dismantled or made to

በቅርቡ ከእስር የተፈቱት ታዋቂው የሲዳማ መብት ተከራካሪ ካላ ዱካሌ ላሚሶ ፍርድቤት እንድቀርቡ ቀጠሮ ተሰጣቸው፤ ሰሞኑን በሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር ውስጥ ኣስራ ሁለት የሹመት መደቦች ሲዳማ ባልሆኑ ግለሰቦች እንዲያዙ ተደረጉ

Image
የሲዳማ መብት ተከራካሪ ካላ ዱካሌ ላሚሶ ከሲዳማ የፊቼ በኣልን ተከትሎ በክልሉ መንግስት መሪነት ከታሰሩት በርካታ የሲዳማ ተወላጆች መካከል የሆኑት እና ከቅርብ ቀናት በፊት የእስር ቤት የተፈቱት ካላ ዱካሌ ሰሞኑን ወደ ፍርድቤት እንድቀርቡ የቀጠሮ ወረቀት ተሰጥቷቸዋል። ስማቸው እንድገለጽ ያልፈለጉ የውስጥ ኣዋቂ ምንጮች ለወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ እንደተናሩት ካለ ዱካሌ ላሚሶ የዩኒቨሪሲቲ ተማሪዎችን በመንግስት ላይ በማነሳሳት፤ ጸረ ኢህኣዴግ / ደኢህዴን ጽሁፎችን በመጻፍ እና በመሳሰሉት ክስ እንደተመረሰረተባቸዋል። እንደእነዚሁ የውስጥ ኣዋቂ ምንጮች ገለጻ ከሆነ፤ የደቡብ ክልል ፕሬዚዴንት ካላ ሽፈራው ሽጉጤ የሲዳማን የክልል ጥያቄ ለመጨፍለቅ በምያደርጉት ጥረት በርካታ የሲዳማ ምሁራንን በማሰር ብሎም በማስፈራራት እያሸማቀቁ የቆዩ ሲሆን፤ ሰሞኑን ከፌደራል እስከ ወረዳ ያሉት የሲዳማ ኣመራሮችን በማሰባሰብ ደኢህዴን ለኣመታት ያልም የነበረውን የሃዋሳን ከተማ ኣስተዳደር ከሲዳማ ተወላጆች እጅ የመንጠቅ ህልማቸውን ኣሳክቷል። የሲዳማ ኣመራሮች ያሳለፉትን ውሳኔ ተከትሎ ሰሞኑን በሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር ውስጥ ኣስራ ሁለት የሹመት መደቦች ሲዳማ ባልሆኑ ግለሰቦች እንዲያዙ ተደርገዋል። የሲዳማን የክልል ጥያቄ የምደግፉት ሆነ የሃዋሳን ከተማ ከሲዳማ እጅ መውጣቱን የምቃወሙትን የሲዳማ ተወላጆች ላይ የሚደርሰው የቃላት ዛቻ ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን፤ ካላ ዱካሌ ፍርድቤት እንድቀርቡ ልደረጉ ያሉት ውስጥ ውስጡን በመቀጣጠል ላይ ያለውን ህዝባዊ ተቃውሞ ለመቀልበስ ታስቦ መሆኑን እነዚሁ ውስጥ ኣዋቂ ምንጮች ኣብራርተዋል።

የሀዋሣ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የማስፈፀም አቅሙን ከፍ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጡ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡

Image
የሀዋሣ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የማስፈፀም አቅሙን ከፍ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጡ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡ በ2ዐዐ4 በጀት አመት በከተማ አስተዳደሩ የተሻለ አፈፃፀም ካስመዘገቡ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የሀዋሣ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የአገልግሎት አሰጣጡን ተደራሽ ለማድረግና የተሻሻሉ አሰራሮች ተግባራዊ እንዲሆኑ እስከታችኛው የመስሪያ ቤቱ መዋቅር ድረስ ሂስና ግለሂስ አድርጓል፡፡ በግምገማው ወቅት እንደተጠቆመው ማዘጋጃ ቤት በባህሪው አገልግሎት ሰጪ ተቋም አንደመሆኑ መጠን በሰራተኛው የአመለካከት ችግርና የክህሎት ክፍተት ምክንያት ሙሉ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት አልተቻለም፡፡ እንደ አቶ ዮናስ ዮሴፍ የሀዋሣ ከተማ ከንቲባ ገለፃ ከከተማ ልማት ስራዎቻችን መካከል ተጠቃሹ የከተማ ነዋሪውን የአገልግሎት ፍላጎቶች ተደራሽ ማድረግ ሲሆን ለዚህም የሲቪል ሰርቫንቱን የአፈፃፀም አቅምና አመለካከቱ ትልቅ ግምት የሚሰጠው ነው ብለዋል፡፡ አቶ ብሩ ወልዴ የሀዋሣ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች ዋና ሥራ አስኪያጅ በበኩላቸው ምንም እንኳን ባለፈው በጀት አመት ማዘጋጃ ቤቱ በተለያዩ የሀገርና ክልል አቀፍ መድረኮች ተሸላሚ ያደረጉትን ስራዎች እንደሰራ ቢታወቅም ይህ ማለት ግን የአገልግሎት አሰጣጡ ሙሉ ነው ማለት አይደለም፡፡ ስለሆነም ያለብንን የአሰራር ክፍተቶች እስከታችኛው መዋቅር ድረስ በመገምገም የተሸለ አፈፃፀም እንዲኖረን ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡ ማዘጋጃ ቤቱ ከዚህ ጐን ለጎን በ2ዐዐ4 በጀት አመት በአገልግሎት አሰጣጣቸው፣ በመረጃ አያያዛቸውና ከዋናው ማዘጋጃ ቤት ጋር ባላቸው የአሰራር ግልፀኝነት በከተማዋ ከሚገኙ 8 ክፍለ ከተሞች የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማን አንደኛ የመናኸሪያ ክፍለ ከተማን ሁለተኛ እንዲሁም የታቦር ክፍለ ከተማን