Posts

Sidama Libration Front -የሲዳማ ነፃ ኣውጭ ድርጅት ኣላማዎች እና በሲዳማ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ከድርጅቱ መሪ ከኣቶ ቤታና ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ

Image
Seife Nebelbal Radio, April 20, 2012, Interview: Asli Oromo and Sidama Liberation leader Kaala Betana የሲዳማ ነፃ ኣውጭ ድርጅት ኣላማዎች እና በሲዳማ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ከድርጅቱ መሪ ከኣቶ ቤታና ጋር  የተደረገ ቃለ ምልልስ ከ 24 ደቂቃ ጀምረው ያዳምጡ::

መድኃኒትና ንብረት የዘረፉ ክስ ተመሠረተባቸው

Image
ፈንድ አቅርቦት ኤጀንሲ የሃዋሳ ቅርንጫፍ የጥበቃ ሠራተኛ የነበረው ግለሰብና ሌሎች ስድስት ግለሰቦች በመመሳጠር ከኤጀንሲው የመድኃኒት ማቆያ መጋዘን ውስጥ ከ1ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት መድኃኒት በመዝረፍ በከባድ የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል ተከሰሱ። የፌዴራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በግለሰቦቹ ላይ የመሠረተው ክስ እንደሚያመለክተው የኤጀንሲው የጥበቃ ሠራተኛ የነበረ 1ኛ ተከሳሽ የመንግሥትን ንብረት እንዲጠብቅ የተሰጠውን ኃላፊነት ወደጎን በመተው ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለራሱ እና ለግብረ አበሮቹ ለማስገኘት በማሰብ ለሕዝብ አገልግሎት ይውሉ የነበሩትን መድኃኒቶች፣ ኬሚካሎች፣ የሕክምና መሣሪያዎች እንዲዘረፉ በማድረጉ ከባድ የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል ፈጽሟል። የኤጀንሲው ሠራተኞች ያልሆኑት ከ2ኛ እስከ 6ኛ ያሉ ተከሳሾች ከ1ኛ ተከሳሽ ጋር ተመሳጥረው መድኃኒት የተከማቸበትን መጋዘን ቁልፍ በመስበር መድኃኒቱ የሚጫንበትን ተሽከርካሪ በማዘጋጀት መድኃኒቱን ከመጋዘን አውጥተው በመጫን እንዲሁም መድኃኒቱ የሚራገፍበትን ቦታ በማመቻቸት በወንጀሉ ድርጊት ሙሉ ተሳታፊና በወንጀሉ የተገኘውን ውጤት ተካፋይ መሆናቸውን የክስ መዝገቡ ያስረዳል። 7ኛ ተከሳሽ የሆነው የኤጀንሲው የጥበቃ ተከሳሽ ዘረፋው በተፈጸመበት ዕለት ተረኝነቱን ሳይጠብቅና የሙያ ግዴታውን በአግባቡ ሳይፈጽም ሌሊቱን ጥበቃ ላይ የነበረ በማስመሰል በሰዓት መቆጣጠሪያ ላይ በመፈረሙ በፈጸመው የሥራ ኃላፊነትን ባለመወጣት የሙስና ወንጀል ተከስሷል። በአጠቃላይ ሁሉም ተከሳሾች በግብረአበርነት በፈጸሙት የሙስና ወንጀል ግምቱ 1ነጥብ7ሚሊዮን ብር የሚያወጣ መድኃኒት ኬሚካሎች ሰፕላይስ እና የሕክምና መሣሪያዎችን በመዝረፋቸው ኮሚሽኑ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ች

በሲዳማ ዞን ይርጋአለም ከተማ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከስድስት መቶ ሺህ ብር በሚበልጥ ገንዘብ ለህዳሴው ግድብ ግንባታ ቦንድ ለመግዛት ቃል ገቡ፡

በሲዳማ ዞን ይርጋአለም ከተማ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከስድስት መቶ ሺህ ብር በሚበልጥ ገንዘብ ለህዳሴው ግድብ ግንባታ ቦንድ ለመግዛት ቃል ገቡ፡፡ በከተማው በፎቶና ቪዲዮ ስራ የሚተዳደሩት አቶ ናአሚን ፍረሕይወት በበኩላቸው የ5 ሺህ ብር ቦንድ ገዝተው በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ከፍለው ለማጠናቀቅ ቃል ገብተዋል፡፡ በሌላም በኩል በሸቀጣሸቀጥ ንግድ ስራ የተሰማሩት ወ/ሮ አበባየሁ ለገሰ የ3 ሺህ ብር ቦንድ የገዙ ሲሆን አምስት መቶ ብር ስጦታ መለገሳቸውንም ገልፀዋል፡፡ የከተማው ከንቲባ አቶ ወንድወሰን ቦልካ ጉዳዩን አስመልክተው እንደገለፁት የግድቡን ስራ ከዳር ለማድረስ የከተማው ህብረተሰብ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት በተለያዩ ጊዜያት ሰፊ የገንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ በየጊዜው በተደረገው ውይይት በከተማው የሚኖሩ ነጋዴዎች፣ የሐይማኖት ተቋማትና ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ቦንድ ለመግዛት ቃል መግባታቸውን የገለፁት ከንቲባው በቃላቸው መሰረት ግዥውን በመፈፀም ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ ሪፖርተራችን መለሰ ሱኩሌ ከበንሳ ቅርንጫፍ ጣቢያ እንደዘገበው፡፡

በሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ቦንድ መግዛታቸውን የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ፡

በሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ቦንድ መግዛታቸውን የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ለገሰ ላሺ እንደገለፁት በቦንድ ግዥው የተሳተፉት በወረዳው 33 የገጠር ቀበሌያትና 4 ከተሞች የሚኖሩ የተለያዩ የእምነት ተቋማት፣ እድሮች እንዲሁም ሞዴል አርሶ አደሮችና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ናቸው፡፡ በተለይም የተፈሪ ኬላ ከተማ ነዋሪዎች የ41 ሺህ 45ዐ ብር ቦንድ እጅ በእጅ ክፍያ በመግዛት ቀዳሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የወረዳው ደህኢዴን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አበበ ዘዳግም በበኩላቸው ህብረተሰቡ ከ5ዐ እስከ 1ዐዐዐ ብር ዋጋ ያለውን ቦንድ ግዥ መፈፀሙን ገልፀዋል ሲል የዞኑ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ዘግቧል፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/05MiyaTextN704.html

በሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ በህዝብ የሚመራ የጤና ልማት ስራ እያከናወነ መሆኑን የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ በህዝብ የሚመራ የጤና ልማት ስራ እያከናወነ መሆኑን የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ ለዚሁም ጽህፈት ቤቱ በ16ቱ ጤና ኤክስቴንሽን ፖኬጆች ዙሪያ አዲስ የትግበራ ስልት በመንደፍ ለጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች ለባለሙያዎችና ለሱፐርቫይዘሮች ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡ በጽህፈት ቤቱ በሽታ መከላከልና ጤና ማጐልበት ዋና ስራ ሂደት ኦፊሰር አቶ ማቴዎስ ማልጌ በወረዳው የትግበራ ስልቱን ውጤታማ ለማድረግ በሁሉም ቀበሌያት የጤና ልማት ሰራዊት መገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በዋናነትም የእናቶችና ህፃናት ሞትን ለመቀነስ እንደሚሰራ ጠቁመው በዚሁ መሰረት ነፍሰጡር እናቶች በወረዳው በሚገኙ ጤና ጣቢያዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ግንዛቤ በማስጨበጥ ረገድ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ብለዋል፡፡ የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሸን ጉዳዮች ጽሀፈት ቤት እንደዘገበው፡፡