Posts

በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ ከ16 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበልግ ይለማል

Image
New አዋሳ, የካቲት 23 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በሲዳማ ዞን የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆነችው ቦርቻ ወረዳ በተያዘው የበልግ ወቅት ከ16 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት እየተሰራ ነው፡፡ ከልማቱም ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ የወረዳው አስተዳደር አስታውቋል፡፡ አርሶ አደሮቹ በበኩላቸው የተለያዩ ግብዓቶችን በመጠቀም ምርታማነታቸውን ለማሻሻል በመስራት ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አማኑኤል አዴላ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በወረዳው ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ሁሉም አርሶ አደር ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሰራ ነው፡፡ በወረዳው ከሚሰበሰበው ምርት 70 በመቶ ያህሉ በበልግ ወቅት ከሚለማ መሬት የሚገኝ በመሆኑ ለበልግ እርሻ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ የእርሻ ሥራ በመከናወን ላይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ታዲዮስ ነዲ በበኩላቸው ዘንድሮ 16 ሺህ 614 ሄክታር መሬት በቦሎቄ፣ በበቆሎ እና በተለያዩ ስራስሮችና ዓመታዊ በሆኑ የተክል ዓይነቶች እንደሚሸፈን ገልፀዋል፡፡ በዘንድሮው በልግ በልዩ ልዩ ዘር ከሚሸፈነው መሬት ከ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል፡፡ የተያዘውን ዕቅድ ለመሳካት ከወረዳ እስከ ቀበሌ ባለው መዋቅር ከሚገኙ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የግብርና ባለሙያዎችና ከህብረተሰቡ ጋር ውይይት መደረጉን ገልፀዋል፡፡ ጽህፈት ቤቱ ከደቡብ ክልል ምርጥ ዘር አቅርቦት ድርጅት ጋር በመቀናጀት ከ1ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 850 ኩንታል ምርጥ ዘር ተገዝቶ ለአርሶ አደሩ መቅረቡንም ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም 37 ሺህ 700 ኩንታል በ

የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የነበሩት አቶ ሽብቁ ማጋኔ በክልሉ ጸረ ሙስና ኮሚሽን በቀረበ ጥያቄ መሰረት ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ተደረገ

የደቡብ ክልል ምክር ቤት ጉባኤ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ትናንት ማምሻውን ተጠናቀቀ ሃዋሳ, የካቲት 21 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - የደቡብ ክልል ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ከ183 ሚሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት በማጽደቅ፣ አራት ዳኞችን ከሀላፊነታቸው በማንሳትና የአንድ የምክር ቤት አባል ያለመከሰስ መብት በማንሳት ትናንት ማምሻውን ተጠናቋል፡፡ ጉባኤው በትናንት ውሎው ባለፉት ስድስት ወራት በክልሉ በተከናውኑ በትምህርት፣ በመንገድ፣ በጤናና ግብር አሰባሰብ ላይ በመወያየት የስድስት ወራት የክልሉን መንግስት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አጽድቋል። ምክር ቤቱ በበጀት ዓመቱ በቀጣይ በ15 ወረዳዎች ለሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ፣ በ10 ወረዳዎች አዲስ ለሚጀመሩ ፕሮጀክቶች፣ ለትምህርት፣ ለጤና፣ ለግብርናና ለክልል ቢሮዎች ለመደበኛና ለካፒታል በጀት ማሟያና ለመጠባበቂያ 183 ሚሊዮን 869 ሺህ 652 ብር ተጨማሪ በጀት አጽድቋል። ጉባኤው የተሰጣቸውን የዳኝነት ስልጣን ተገን በማድረግ በግለሰቦች ላይ በደል ፈጽመዋል የተባሉትን የአርባምንጭ አካባቢ ጋማ ፍርድ ቤት ዳኛ አቶ ስንታየሁ ለማ፣ በጌድዮ ዞን የቡሌ ወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛ አቶ ፍላሳ ቡርቃ፣ የቦዲቲ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኛ አቶ ፋንታ ቤርቦና የከፋ ዞን ጠሎ ወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛ አቶ አደመ አርጋጎ ከኃላፊነታቸው በማንሳት ጉዳያቸው በህግ እንዲታይ ወስኗል። በሌላ በኩል ደግሞ አቶ ሙሉጌታ አጎን የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት አድርጎ ሲሾም 24 አዲስ የወረዳ፣ የዞንና የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመት አጽድቋል። ምክር ቤቱ ትናንት ማምሻውን ሲጠናቀቅ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የነበሩት አቶ ሽብቁ ማጋኔ በክልሉ ጸረ ሙስና ኮሚሽን በቀረበ ጥያቄ መሰረት ያለመከሰስ መብታቸው እን

PCI Receives Starbucks Foundation Grant For Sidama Coffee Farmers

New Two-year, $500,000 grant will improve health through clean water, sanitation and hygiene project San Diego, CA (PRWEB) February 27, 2012 PCI (Project Concern International) announced today it has received a $500,000 grant from the Starbucks Foundation for its Sidama Coffee Farmers Health through Water, Sanitation and Hygiene Project. The project is designed to improve the health outcomes of coffee farmers and their communities in two high-need areas in the Sidama Zone of Southern Ethiopia. The grant is part of a long-term commitment by Starbucks and the Starbucks Foundation to support relevant local needs in coffee growing communities and a continuation of supporting integrated water and sanitation programs. In Ethiopia, coffee farming is the primary source of income for many rural households, which also have some of the lowest coverage of water access, sanitation and hygiene (WASH) facilities and systems in Sub-Saharan Africa. Contamination of water sources from coffee w

Documentary - Fiche - Sidama new year

New http://www.ethiotube.net/video/15783/Documentary--Fiche--Sidama-New-Year  

በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የቻይና ቋንቋ ትምህርት ፕሮግራም ሊጀመር ነው

Image
New አዋሳ, የካቲት 16 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የቻይና ቋንቋ ትምህርት ፕሮግራም ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን የዩኒቨርስቲው ሶሻል ሳይንስና ሂዩማኒቲ ኮሌጅ ዲን ገለጹ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሚከፈተውን የትምህርት ፕሮግራም ምክንያት በማድረግ በቻይና ኖርዝ ዌስት ኖርማን ዩኒቨርስቲ የተዘጋጀ የቻይና የባህል ትርኢት ትናንት ማምሻውን ተካሄዷል፡፡ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ በተካሄደው ስነ ስርዓት ላይ የዩኒቨርስቲው የሶሻል ሳይንስና ሂዩማኒቲ ኮሌጅ ዲን ዶክተር ንጉሴ መሸሻ እንደገለጹት የቻይና ቋንቋ ትምህርት ፕሮግራምን በሚቀጥለው ሳምንት ለመጀመር የሚያስችል በኮሌጁ የቋንቋዎች ጥናት ክፍል ከ600 በላይ ኢትዮጵያን ተማሪዎች ተመዝግበዋል፡፡ ለመማር ማስተማሩ ስራ የሚስፈልጉ መጻህፍትና መምህራንን ጨምሮ አስላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸው አዲስ አበባ ከሚገኘው የቻይና ኮፊሸንስ ኢንሰቲትዩት ጋር ከዚህ ቀደም ሲል ባደረጉት የመግባባያ የጋር ስምምነት መሰረት በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የቻይና ቋንቋ ማዕከል ተከፍቷል ብለዋል፡፡ ቀደም ሲልም አንድ የዩኒቨርስተው የስራ ሃላፊ በቻይና የልምድ ልውውጥና ጉብኝት ማድረጋቸውን ጠቁመው ዩኒቨርሰቲዎች ከዩኒቨርሰቲዎች ጋር የትብብር ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተመሳሳይ የግንኙነት ፕሮግራም እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡ የባህል ቡድኑን በመምራት የቻይናው ኖርዝ ዌስት ኖርማን ዪኒቨርስቲ ምክትል ፕሬዝዳንት መምጣታቸው የትብብር ግንኙነቱን የበለጠ እንደሚያጠናክረው ዶክተር ንጉሴ አስታውቀው ቻይናና ኢትዮጵያ በፖለቲካ፣በኢኮኖሚ፣ በባህል፣ በዲፕሎማሲና ሌሎችም ዘርፎች ግንኙነታቸው ተጠናክሮ ጥምረት መፍጠራቸውን እንደሚያሳይ ገልጠዋል፡፡ የቻይና ኢኮኖሚ እያደገ