Posts

Including Moges Tadess(Sidama coffee) Ethiopia intensify Nigeria preparations

Image
Ethiopia's preparations are in top gear after the arrival of Finland based Fuad Ibrahim in camp ahead of the do or die Nigeria return leg on the 16th November. Despite the cancellation of an intended friendly against Burkina Faso coach Sewnet Bishaw has been conducting training in Addis Ababa with 23 players in camp . Bishaw is delighted that the morale in camp was upbeat and he was happy with the training programme. He told supersport.com that: "The mood in the camp is very positive it was disappointing for the Burkina Faso friendly to be cancelled but sometimes this things happen. Our focus is on ahead of the Nigeria game as I always believe anything is possible and we will work on our mistakes " "It will be a tough match in Nigeria but the truth is that we will fight for the entire 90 minutes as we intend to cause an upset " he added. Players in Camp : Samson Assefa{Gk} 2.Degu debebe ,Saladin Bargicho ,Biyadgelg Eliyas ,Abebaw Butako ,Mentesn

ተግባር! ተግባር! አሁንም ተግባር!

በተጠናቀቀው ሳምንት የአፍሪካ መገናኛ ብዙኃን ባለቤቶች፣ መሪዎችና ጋዜጠኞች በመዲናችን በአዲስ አበባ ባካሄዱት ስብሰባ የአፍሪካ ሚዲያ ያለፉት የሃምሳ ዓመታት ጉዞ ምን ይመስላል? ቀጣዩስ መሆን አለበት? በሚል አጀንዳ ላይ ተወያይተዋል፡፡ ወደ ኢትዮጵያ አትሂዱ፣ ይህንን ስብሰባ በኢትዮጵያ አታካሂዱ የሚለው የተለመደው የፅንፈኛ ዳያስፖራ ፖለቲከኞች ተቃውሞ በበረታበት አፍሪካውያን የለም ወደ ኢትዮጵያማ እንሄዳለን፣ በመወያየት እንጂ በማኩረፍና በጥላቻ አናምንም ማለታቸውና መምጣታቸው ለኢትዮጵያም፣ ለአፍሪካም፣ ለሚዲያውም ትክክለኛ ውሳኔ ነበር፡፡ ውጤታማም ነበር፡፡ በዚህ ስብሰባ ላይ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ተግባር በኢትዮጵያ በኩል ተከናውኗል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በስብሰባው የመክፈቻ ንግግራቸው መንግሥት የኢትዮጵያን ሚዲያ ለማሻሻልና ለመለወጥ ዝግጁ መሆኑን ብቻ ሳይሆን፣ የለውጥ ዕርምጃ በቅርቡ እንደሚጀምር አብስረዋል፡፡ ተሳታፊዎችም በተስፋና በደስታ ተቀብለውታል፡፡  የሕዝብ ተሳትፎ እውን ሊሆን የሚችለው መረጃ ያለው ኅብረተሰብ ሲኖር እንደሆነ ገልጸው፣ መረጃ ያለው ኅብረተሰብ እውን የሚሆነውም ጠንካራ ሚዲያ ሲኖር መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል፡፡  አሁን ያለውን የኢትዮጵያ ሚዲያ ችግር በመገምገምና የመፍትሔ ሐሳብ በማስቀመጥ የሚወሰደው የለውጥ ዕርምጃ በዘፈቀደና በግምት የሚደረግ ሳይሆን፣ ከሚዲያ ባለሙያዎች፣ ከሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎችና ከሚመለከታቸው አካላት በሚገኝ ገንቢ ሐሳብ መሠረት እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸው፣ ለውጡ በቅርቡ  በተግባር እንደሚጀመር ቃል ገብተዋል፡፡  የተገባውን ቃል በተግባር ለማየት በጉጉት እንጠብቃለን፡፡ በነገራችን ላይ ይህ የተገባው ቃል ማጠናከሪያና ተጨማሪ ማስተማመኛ እንጂ፣ ኢት

በመልካም አስተዳደር ከ52 የአፍሪካ አገራት ኢትዮጵያ 33ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች

Image
ከ11 የምስራቅ አፍሪካ አገራት ደግሞ በ8ኛ ላይ ተቀምጣለች መልካም አስተዳደር ከ100% ሞሪሺየስ - 80 ቦትስዋና - 78 ኬፕቨርዴ - 77 ሲሸልስ - 78 ደቡብ አፍሪካ - 71 ሶማሊያ - 8 የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን የ2013 የመልካም አስተዳደር ውጤታማነት ደረጃን “Ibrahim Index of African Governance (IIAG)” ይፋ ያደረገው ከሁለት ሳምንት በፊት ነበር፡፡ በመልካም አስተዳደር ምርጥ ተብላ ከአፍሪካ በአንደኝነት ደረጃ የተቀመጠችው ሞሪሺየስ ስትሆን የመጨረሻዋ አገር ሶማሊያ ናት፡፡ ኢትዮጵያ ከ52 የአፍሪካ አገራት 33ኛ ደረጃ ተሰጥቷታል፡፡ በኢትዮጵያ ያለውን የመልካም አስተዳደር ሁኔታ በአራት መስፈርቶች የገመገመው የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን፤ ባለፉት 10 ዓመታት በሰው ሃብት ልማት ላይ ከፍተኛ መሻሻል መታየቱን ገልፆ፤ በዋናነት በጤና እና በትምህርት መስኮች ለውጥ መመዝገቡን አመልክቷል፡፡ ኢትዮጵያ በመልካም አስተዳደር ከ52 የአፍሪካ አገራት 33ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው ከ100 ነጥብ 47.6 በማግኘት ሲሆን የአፍሪካ አማካይ ነጥብ 51.6 ነው ይላል ፋውንዴሽኑ፡፡ ኢትዮጵያ ከ11 የምስራቅ አፍሪካ አገራት ጋር ተወዳድራም በ8ኛ ደረጃ ላይ እንደተቀመጠች የጠቆመው የፋውንዴሽኑ መረጃ፤ በዚህ የአፍሪካ ቀጠናም ኢትዮጵያ የሚጠበቀውን የ47.9 አማካይ ነጥብ አለማግኘቷን አመልክቷል፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት 10 ዓመታት በመልካም አስተዳደር ያላትን ደረጃ ያሻሻለችው በ5.1 ብቻ ነው ይላል፤ መረጃው፡፡ የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን “ኢብራሂም ኢንዴክስ ኦፍ አፍሪካን ጋቨርናንስ” ሪፖርት፤ የአፍሪካ አገራት በአጠቃላይ በመልካም አስተዳደር መሻሻል እንዳሳዩ ጠቁሟል፡፡ አገራቱ የተመዘኑት የመልካም አስተዳደር መገለጫ ናቸው ተብለው በሚታ

የሰብዓዊ መብት አፈጻጸምን የሚከልሰው ዕቅድ

ዕውቁ ኖርዌያዊው ተመራማሪ ሼትል ትሮንቮል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) በኢትዮጵያ ላይ ያወጣውን ሪፖርት ተመርኩዞ፣ ‹‹Human Rights Violations in Federal Ethiopia: When Ethnic Identity is a Political Stigma›› በሚል ርዕስ በ2000 ዓ.ም. አንድ የምርምር ጽሑፍ አሳትመው ነበር፡፡ ተመድ በ1999 ዓ.ም. ያወጣው ሪፖርት በኢትዮጵያ ብሔርን መሠረት ያደረገ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደሚፈጸም ይከሳል፡፡ ፕሮፌሰር ትሮንቮል በጥናታቸው የተመድ ሪፖርት ድምዳሜ ትክክል እንደሆነ ይከራከራሉ፡፡  በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት መምህር የሆኑት አቶ ጌታቸው አሰፋ ለትሮንቮል በጻፉት የታተመ ምላሻቸው በኢትዮጵያ መንግሥት የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እንደሚደረግና የመብት ጥሰቱ ክስ ስህተት እንደሆነ፣ ጥሰት አለ ከተባለም ብሔርን መሠረት ያደረገ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደማይፈጸም ተከራክረዋል፡፡ በ2001 ዓ.ም. ለንባብ በበቃው ምላሻቸው አቶ ጌታቸው እንደ ሼትል ትሮንቮል ያሉ የውጭ አገር ተመራማሪዎች ስለ ኢትዮጵያ ማኅበራዊ፣ ሕጋዊና ፖለቲካዊ ውስብስብ ጉዳዮች በድፍረት ለማሳተም ለራሳቸው ነፃነት የሚሰጡት፡ በአገሪቱ ጥቂት ቀናትን በዛ ካለም ወራትን ካሳለፉ በኋላ መሆኑን ተችተው ነበር፡፡ እነዚህ ተመራማሪዎች በውጭ ጸሐፍት የተጻፉ የምርምር ሥራዎችን ብቻ በማጣቀስ ከባድ ድምዳሜ ላይ እንደሚደርሱም አመልክተዋል፡፡  ፕሮፌሰር ትሮንቮል ለአቶ ጌታቸው ምላሽ በሰጡት ሌላ ምላሽ ስለኢትዮጵያ ከአቶ ጌታቸው የተሻለ ግንዛቤ እንዳላቸው ገልጸው ነበር፡፡ የመመረቂያ ጽሑፋቸው በኢትዮጵያ የእርስ በርስ ጦርነት ላይ እንደነበር ያሰታወሱት ትሮንቮል፣ ከ1980ዎቹ መጀመሪያ ጀምረው በኢትዮጵያ ስላለው የፖለቲካና

ቡና ለመጠጣት ተመራጩ ሰዓት - ዘ ቴሌግራፍ

Image
ቡና በመጠጣት በአነቃቂው ንጥረ ነገር አማካኝነት ውሎዎን ነቃ ብለው ለማሳለፍ ከፈለጉ ተመራጩ ሰዓት ከጠዋቱ 3፡30 እስከ 5፡30 ያለው ነው ሲሉ የነርቭ ስርዓት ተመራማሪዎች የገለጹት፡፡ አንድ ሲኒ አሪፍ ቡና ከምንም ነገር በፊት በጠዋት መጠጣት ጥሩ     ቢሆንም ትንሽ ረፈድ ሲል መጠጣቱ ደግሞ የበለጠ ጥሩ ነው ብለዋል በዘርፉ ጥናት ያከናወኑ ሳይንትስቶች፡፡ ይህም የሆነው ኮርቲሶል የተባለውና ሰውነትን ለመቆጣጠር የሚረዳው ዋናው ሆርሞናችን ከቡናው ንጥረ-ነገር ካፌን ጋር በሚኖረው መስተጋብር ውስጣዊ ሰርዓቱንና መነቃቃትን ስለሚያግዝ ነው ተብሏል፡፡ በደማችን ውስጥ የሚኖረው ኮርቲሶል ከእንቅልፍ በነቃን ቅጽበት መጠኑ ከፍተኛ ሲሆን ለአንድ ሰዓት ያህል ማለትም በአማካኝ ከጠዋቱ 2 እስከ 3 ሰዓት ድረስ ከፍተኛ ሆኖ ይዘልቃል፡፡ ኮርቲሶል መመንጨት ዝቅ በሚል ሰዓት ማለትም ረፈድ ሲል ቡና መጠጣቱ አዋጭ ነው ይላሉ በቤተሳይዳ ሜሪላንድ የጤና ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ የነርቭ ስርዓት ተመራማሪው ስቴቨን ሚለር፡፡ የኮርቲስል ሆርሞን ከፍተኛ ደረጃ ላይ ባለበት ጊዜ ቡና መጠጣቱ ግን የቡናውን አነቃቂ ንጥረ ነገር ካፌንን እንዲላመዱት ያደርጋል፡፡ ይህ ደግሞ ሌላ ተጨማሪ ማነቃቂያ እንዲፈልጉ ሊያደርግ ይችላል ብለዋል ስቴቨን፡፡ ሌሎች ተመራማሪዎች ደግሞ ከሰዓት በኋላ ቡና መጠጣት ከምሳ በኋላ የሚከሰተውን ቀልብ ያለመሰብሰብ ችግር ይፈታል ይላሉ፡፡ ስቴቨን ሚለር በደማችን የሚኖረው የኮርቲስል መጠን ምሽት 1 ሰዓት እና ከ11፡30 እስከ 12፡30 ባሉት ሰዓታትም   እንደሚጨምር   ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ትክክለኛው የቡና መጠጫ ሰዓት ይህ ነው ለማለት እንደሰዎቹ የኮርቴስል መጠን የመጨመርና መቀነስ ሂደትና ከእንቅልፋቸው እንደሚነሱበት ሰዓት ከሰው ሰው እንደሚለያ

Land Grabs In Africa – A Double-Edged Sword

Image
VENTURES AFRICA – Foreign investors are taking as much as they can from an impoverished nation, including its crops, land and the hard work of an Ethiopian population, to serve their own interests above others. According to the Food and Agriculture Organisation (FAO), 14.56 million hectares of Ethiopia’s 100 million hectare land mass is arable land, most of it cultivated by small hold, subsistence farmers. International investors have taken note and are rushing to this country, once synonymous with starvation, to take advantage of the government’s new push to improve its agricultural production capacity. But many fear the government’s sale of arable land to foreign nationals will create a modern form of agricultural colonialism. One such arrangement, launched in 2009 under Saudi Arabia’s King Abdullah initiative and forming part of a $100-million investment scheme in Ethiopian agriculture, had farmers grow teff (a North African cereal grass), white wheat, maize and white sorghum,

ኢትዮጵያውያን የመንግስትን ስለላ አይፈሩም፤ ሁለመናቸው በመንግስት እጅ ነው

የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ አለምን ከዳር ዳር በሚያዳርስ የመረጃ መረብ፣ የውጭ ዜጎችን (የጠቅላይ ሚኒስትሮችና የፕሬዚዳንቶች ጭምር) የስልክና የኢሜይል ልውውጦችን የቱን ያህል በስፋት እንደሚሰልል ሲታይ ጉድ ያሰኛል። በእርግጥ የስለላ ተቋሙ የአሜሪካ ዜጐችን በዘፈቀደ አልሰልልም ብሏል፡፡ የዜጐች የግል ሕይወትና የመልእክት ልውውጥ በመንግስት መነካት እንደሌለበት በአገሪቱ ሕገመንግስት ታውጇላ። የዜጐችን የስልክ እና የኢሜይል መልእክት የምበረብረው፣ በተጠርጣሪዎች ላይ በማተኮርና ፍርድ ቤትን በማስፈቀድ ብቻ ነው ይላል - የአሜሪካ የስለላ ተቋም። ታዲያ “ፍርድ ቤት” ሲባል፣ የወትሮው አይነት አይደለም። በሚስጥር የሚሰራ ልዩ ፍርድ ቤት ነው። ማዘዣ ወረቀቱም በሚስጥር የሚጠበቅ ስለሆነ፣ ከጊዜ በኋላ የፍርድ ቤቱን ውሳኔዎችና ትዕዛዞች መመርመር ያስቸግራል። ፍርድ ቤትን ማስፈቀድ በኢትዮጵያ አይሰራም በእውነቱ፣ እንዲህ አይነቱ ድብቅ የፍርድ ቤት አሰራር፣ ከታላቋ የነፃነት አገር (ከአሜሪካ) የሚጠበቅ አይደለም። ለማንኛውም፣ የስለላ ተቋሙ “የፍርድ ቤት” ማዘዣ በማቅረብ ባለፉት አምስት አመታት የተለያዩ መረጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል፡፡ ጉግል፣ ያሁ፣ ሆትሜይል፣ ፌስቡክ እንዲሁም ኤቲኤንድ ቲ የመሳሰሉ የኢንተርኔት እና የስልክ ኩባንያዎችም፣ የመቶ ሺ ገደማ ደንበኞች መረጃ ለስለላ ተቋሙ ለማስረከብ መገደዳቸውን ገልፀዋል። ኩባንያዎቹ የሕግ ግዴታ ሆኖባቸው እንጂ፣ የአንድም ሰው መረጃ አሳልፈው መስጠት አይፈልጉም - እንጀራቸው ነዋ። በደንታ ቢስነት የደንበኞችን መረጃ እያወጣ ለመንግስት የሚዘረግፍ ኩባንያ፣ የቱንም ያህል ግዙፍ ቢሆን መንኮታኮቱና በአጭር መቀጨቱ አይቀርም። ደንበኞቹ ይሸሹታል፤ ፊታቸውን ወደ ሌላ አገልግሎት ሰጪ ኩባንያ በማዞር ጀርባቸውን ሲሰጡት፣ በኪሳራ ይፈራር

የገዛኸኝና እልፍነሽ ሆቴልና ሪዞርት በዱላ ቅብብል ውድድር ይመረቃል

Image
ማራቶን የማዘጋጀት ሃሳብ አላቸው                 በሀዋሳ ከተማ የተገነባውን ገዛኸኝና እልፍነሽ ሆቴልና ሪዞርት ህዳር 14 በይፋ ሲመረቅ ልዩ የ10 ኪሎሜትር የዱላ ቅብብል ውድድር እንደሚካሄድ ታወቀ፡፡ በምረቃው ስነስርዓት ላይ በክብር እንግድነት እንዲገኙ ኡጋንዳዊው የኦሎምፒክ እና የዓለም ሻምፒዮን የማራቶን ድርብ አሸናፊ ስቴፈን ኪፕሮች እና ኬንያዊ አትሌት ጄፈሪ ሙታይ ተጋብዘዋል፡፡ በሌላ ዜና ባልና ሚስቶቹ ማራቶኒስቶች አትሌት ገዛኸኝ አበራ እና አትሌት እልፍነሽ አለሙ በሚቀጥለው ዓመት አንድ የማራቶን ውድድር በኢትዮጵያ ለማዘጋጀት ማሰባቸውን ሲያስታወቁ ተተኪ አትሌቶችን ለማግኘት የአገር ውስጥ ውድድሮች መብዛታቸው አስፈላጊ እንደሆነ ስላመኑበት የነደፉት እቅድ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ አትሌት ገዛኸኝ አበራ እና አትሌት እልፍነሽ አለሙ ትናንት በዋና ፅህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ የሆቴልና ሪዞርት ምረቃው ከአትሌቲክስ ውድድር ጋር ማያያዝ ያስፈለገው ተተኪ አትሌቶች የእነሱን አርዓያ እንዲከተሉ ለማነሳሳት በማሰባቸው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ አትሌት እልፍነሽ አለሙ‹‹ ማንኛውም ሰው ዓላማዬ ብሎ ከሰራ ለየትኛውም ደረጃ ይደርሳል፡፡ በአሁን ዘመን ያሉ አትሌቶች ደከመን፣ ሰለቸን፤ ከሳን ፤ ጠቆርን ሳይሉ በትጋት መስራት አለባቸው፡፡ በስፖርቱ እኛ የደረስንበት ስኬት ለማግኘት ብቻ ሳይሆን ከእኛ በላይ ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ማወቅ አለባቸው›› ብላለች፡፡ አትሌት ገዛኸኝ በበኩሉ ‹‹እኛ ሮጠን ሆቴሉን ሰርተናል፤ አትሌቱም እንደማንኛውም ህብረተሰብ በትጋት ከሰራ ይሳካለታል፡፡›› በማለት ተናግሯል፡፡ በሆቴልና ሪዞርቱ ምረቃ ላይ የሚካሄደው የ10 ኪሎሜትር የዱላ ቅብብል ውድድሩ መነሻውና መድረሻው ገዛኸኝና እልፍነሽ ሆቴልና ሪዞርት እንደሆነ የገለፀው አትሌ

አባባ ተስፋዬ - በሐዋሳው ተረት ቤት

Image
“ወጣቶች፤ ሀገራችሁን ውደዱ፤ አንብቡ!”            በሐዋሳ ከተማ ሐይቁ ዳርቻ በሚገኘው “ሌዊ ሪዞርት” የተሰራው “የተረት ቤት” ጥቅምት 23 ቀን 2006 ዓ.ም ተመርቋል፡፡ በኢትዮጵያ የመጀመርያው እንደሆነ የተነገረለት “የተረት ቤት”፤ ለበርካታ አስርት ዓመታት በሬዲዮና በቴሌቪዥን ተረት በመንገር በሚታወቁት የ90 አመቱ አርቲስት ተስፋዬ ሳህሉ (አባባ ተስፋዬ) ስም የተሰየመ ነው፡፡ ባለፈው ሳምንት የተረት ቤቱ ሲመረቅ በክብር እንግድነት የተገኙት አባባ ተስፋዬ፤ “የጥንቸልና የዔሊ ውድድር” የተሰኘ ታሪክ በመናገር ተረት ቤቱ በይፋ ሥራ መጀመሩን ይፋ አድርገዋል፡፡ በምረቃው ዕለት ንግግር ያደረጉት የሌዊ ሪዞርት ባለቤት አቶ ወንድይፍራው እንደሻው፤ የተረት ቤቱን መሰራት አስመልክተው ሲናገሩ፤ “የልጆችን የንባብ ልምድ ለማዳበርና በየሳምንቱ ለልጆች ቁምነገር በተረት መልክ የምናስተላልፍበት ነው” ብለዋል፡፡ ተረት ቤቱ ከቢዝነስ ጋር የተገናኘ አይደለም ያሉት አቶ ወንድይፍራው፤ “በውጭ ፊልሞችና ታሪኮች እየተመሰጡ ላሉ ልጆቻችን ታሪካችንን እና ባህላችንን ለማስተላለፍ አስበን ነው” በማለት የተረት ቤቱን ዓላማ ተናግረዋል፡፡ በአዋሳው የተረት ቤት ምረቃ ወቅት የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ መልካሙ ተክሌ ከአባባ ተስፋዬ ጋር አጭር ቆይታ በማድረግ የልጅነት ሕይወታቸውን ያስታወሳቸው ሲሆን ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የለቀቁበትን ሁኔታና ዳግም የመመለስ ሃሳብ እንዳላቸው እንዲሁም ሌሎች ጉዳዮችን አንስቶ ተጨዋውተዋል፡፡ እነሆ፡- በልጅነትዎ ተረት እየሰሙ ነው ያደጉት እንዴ? ተረት አይደለም በልጅነቴ የተነገረኝ፡፡ ቤተሰቦቼ እርግጡን እየነገሩ ነው ያሳደጉኝ፡፡ ቤተሰባችን ለንጉሣውያን ቤተሰብ ቀረብ ያለ ነው፡፡ የተወለድኩት ባሌ አካባቢ ነው፡፡ ጥሩ ነገር ስለመስራት፣ ትእ

Ethiopia Set to Save Children from Diarrhoea

Ethiopia today launches a program to protect the 2.8 million children born in the country each year with a vaccine against rotavirus, which leads to severe, and often fatal, diarrhoea. The country has one of the greatest burdens of rotavirus anywhere in the world, accounting for 6 per cent of all deaths from the disease globally. Ethiopia is the 17th country to introduce the rotavirus vaccine with GAVI Alliance support, according to UNICEF. “Few things in the world have a greater impact on public health than vaccines,” said GAVI CEO Dr Seth Berkley. “Rotavirus vaccine offers the best hope for preventing the deadly dehydrating diarrhoea caused by this disease and preventing thousands of deaths of young children in Ethiopia.” “Diarrhoea takes the lives of more than 38,500 Ethiopian children under-five each year, rotavirus being responsible for close to two-thirds of the deaths,” said Ethiopia’s Minister of Health Dr Admasu Kesetebirhan. “Providing rotavirus vaccines to our chil

Ethiopia arrests two journalists from independent paper

Image
thiopian police have arrested without charge two editors of the independent Amharic weekly Ethio-Mihdar, according to local journalists. © wellphoto via Fotolia.com Police in the town of Legetafo, north-east of the capital Addis Ababa, on Monday arrested Getachew Worku in connection a story published in October alleging corruption in the town administration, according to Muluken Tesfaw, a reporter with the paper, who spoke to Worku shortly after his arrest. Worku has not been charged, he said. On Saturday, police arrested Million Degnew, the general manager of the newspaper, and Muna Ahmedin, a secretary, said Muluken and local journalists. Ahmedin was released the same day but Degnew remains in custody without charge, Tesfaw said. An intimidation tactic "A free and inquisitive media is a cornerstone of development that should benefit all Ethiopians," said CPJ's Africa Program Coordinator Sue Valentine. "Repeatedly detaining journalists without charge is an in

Ethiopia arrests two journalists from independent paper

Image
thiopian police have arrested without charge two editors of the independent Amharic weekly Ethio-Mihdar, according to local journalists. © wellphoto via Fotolia.com Police in the town of Legetafo, north-east of the capital Addis Ababa, on Monday arrested Getachew Worku in connection a story published in October alleging corruption in the town administration, according to Muluken Tesfaw, a reporter with the paper, who spoke to Worku shortly after his arrest. Worku has not been charged, he said. On Saturday, police arrested Million Degnew, the general manager of the newspaper, and Muna Ahmedin, a secretary, said Muluken and local journalists. Ahmedin was released the same day but Degnew remains in custody without charge, Tesfaw said. An intimidation tactic "A free and inquisitive media is a cornerstone of development that should benefit all Ethiopians," said CPJ's Africa Program Coordinator Sue Valentine. "Repeatedly detaining journalists without charge is an in

IMF: Ethiopian economy needs revamp to avert slowdown

Addis Ababa - Ethiopia's economy has reached a crossroads and, to prevent growth rates from falling, needs to be restructured to encourage more private sector investments, the International Monetary Fund said on Wednesday. Economic output should grow 7.5 percent in each of the next two fiscal years, to July 2014 and 2015, down slightly from the 8.5 percent in 2011/12, Jan Mikkelson, the IMF's representative in Ethiopia, told reporters. It expects year-on-year inflation - which dipped to 6.9 percent in September from 7.0 percent in August - to remain in single digits. The government has reported double-digit GDP growth for much of the past decade, but some economists say those figures are inflated. It said in July it expected the economy to maintain a growth rate of 11 percent in 2013/14. Growth has been propelled by huge public spending on infrastructure, while an expansion in services and agriculture has also boosted the economy. Ethiopia's exports include coff

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የ2005 ዓ.ም ሪፖርት እንደሚያመለክተው በዓመቱ የመጀመሪያ ሦስት ወራት በወባ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ይጨምራል፤

Image
የወባ በሽታና የመከላከል ጥረቶች የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የ 2005  ዓ . ም ሪፖርት እንደሚያመለክተው በዓመቱ የመጀመሪያ ሦስት ወራት በወባ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ይጨምራል፤ ከሁለት ሺ ሜትር በታች በሆኑ የወይና ደጋና ቆላማ አካባቢዎች ሁሉ ይተላለፋል  -  የወባ በሽታ። በአብዛኛው ከክረምት ወራት በኋላ ከመስከረም እስከ ህዳር ባለው ወቅት ስርጭቱ የሚጨምር ሲሆን በአንዳንድ ቦታዎች ከበልግ ዝናብ ተከተሎ ባሉ ወራትም ይከሰታል። ስለ ወባ በሽታ አጠቃላይ ግንዛቤ ለማስረጽ ይረዳ ዘንድ እንዲሁም በሽታውን በመከላከል በኩል ስለሚደረጉት ጥረቶች መረጃ ለማግኘት ወደ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጎራ ብለን ነበር። በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የወባ መከላከልና መቆጣጠር ቡድን መሪ የሆኑት ወይዘሪት ህይወት ሰለሞን ስለወባ በሽታና የመከላከል ጥረቱን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተውናል። « የወባ በሽታ ፕላስሞድየም የሚባል በአይን የማይታይ ረቂቅ ጥገኛ ተህዋስ በደም ውስጥ መኖር፣ ማደግና መራባት ምክንያት የሚከሰት በሽታ ነው። ይህ በሽታ በአለም ላይ በብዙ ቦታዎች ይከሰታል። በአገራችንም ሰባ አምስት በመቶ በሚሆነው የቆዳ ስፋት የወባ በሽታ ይታያል። ስልሳ ስምንት በመቶ የሚሆነው ህዝብም ለበሽታው ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ይገኛል »  ይላሉ ወይዘሪት ሕይወት። የወባ በሽታ አኖፊለሰ በመባል በምት ታወቀው እንስት የወባ ትንኝ አማካኝነት ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፍ ተህዋስ ነው። ትንኟ የምታስተላልፈው የበሽታው መንስኤ የሆነውን ተህዋስ ነው፡፡ በሃገራችን ሁለት ዋና ዋና የወባ ተህዋስ ዝርያዎች አሉ የሚሉት ቡድን መሪዋ ፕላዝሞዲየም ፋልሲፓረም እና ፕላዝሞዲየም ቫይቫክስ በመባል እንደሚ ታወቁ ይናገራሉ። በሽታው አኖፊለስ በመባል በምትታወቀው እንስቷ የወባ