Posts

የስኳር ህመም መንስኤና ጥንቃቄ

Image
የዓለም የጤና ድርጅት የስኳር ህመም ቆሽት የተሰኘዉ የዉስጥ አካል ኢንሱሊን የተባለዉን ተፈላጊ ቅመም በበቂ ማምረት ሲሳነዉ ወይም፤ ቆሽት ያመረተዉን ኢንሱሊን ሰዉነት በአግባቡ መጠቀም ሲያቅተዉ ሊከሰት እንደሚችል ያመለክታል።  እንዲህ ያለዉ እክል ሰዉነትን ሲያጋጥም ደግሞ ደም ዉስጥ በርከት ያለ የስኳር ፈሳሽ/ግሉኮስ/ ይከማቻል። ይህ የመጀመሪያዉ ዓይነት የስኳር ህመም ሲሆን፤ ሁለተኛዉ ዓይነት ደግሞ፤ በተመሳሳይ ሰዉነት ተገቢ ያልሆነ የኢንሱሊን አጠቃቀም ሲኖረዉ የሚከሰት ሆኖ፤ መጠን ያጣ ክብደት ሲኖርና በአግባቡ የሰዉነት እንቅንቃሴ ባለመደረጉ እንደሚከሰት መረጃዉ ያብራራል። የኢትዮጵያ የስኳር ህመም ማኅበር ፕሬዝደንትና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጥቁር አንበሳ ሃኪም ቤት በተለይ የስኳር ህመምን የሚከታተሉት ባለሙያ ዲክተር አህመድ ረጃ ይህ የጤና እክል የእድሜ ዘመን ህመም መሆኑን ያመለክታሉ።   የስኳር በሽታ ታማሚዎች ቁጥር ከመቼዉም ጊዜ በላይ እየጨመረ እንደሚገኝ ጥናቶች እያመለከቱ ነዉ። እንዲያም ሆኖ ጥናቱ እንደሚለዉ የህመሙ ተጠቂ ከሆኑ ግማሽ ያህሉ ገና ተገቢዉን ምርመራ አላደረጉም። የሰዉነት ክብደትን መቆጣጠር ከአንድ ዓመት በፊት 366 ሚሊዮን የነበረዉ በዓለማችን የስኳር በሽታ ታማሚዎች ቁጥር በአሁኑ ወቅት 371 ሚሊዮን መድረሱን በቅርቡ የወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ። ዓለም ዓቀፍ የስኳር ህመም ፌዴሬሽን እንደሚለዉም ከሆነም በጎርጎሮሳዊዉ 2030ዓ,ም ቁጥሩ ወደ552 ሚሊዮን ማሻቀቡ አይቀርም። ቻይና ዉስጥ ብቻ 92,3 ሚሊዮን ህዝብ ለዚህ የጤና ችግር ሲጋለጥ የጤና አገልግሎቱ ባልተስፋፋበት በአፍሪቃም እንዲሁ ቁጥሩ ሊበረክት እንደሚችል ይገመታል። ሸዋዬ ለገሠ ሂሩት መለሰ የስኳር ህመም መንስኤና ጥንቃቄ  

33 የፖለቲካ ድርጅቶች በምርጫ ስም ገንዘብ ማባከን እንዲቆም ጠየቁ

ታህሳስ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ድርጅቶቹ ባወጡት መግለጫ በጥቅምት 15 ቀን 2005 ዓም የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በአዳማ ኤክስኪዩቲቭ ሄቴል በዚህ አመት በሚደረገው የአካባቢ እንዲሁም የአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተማ ምርጫ የግዜ ሰሌዳን አስመልክቶ  የውይይት መድረክ መጥራቱን ጠቅሰዋል። ድርጅቶቹ በመግለጫቸው ” ምርጫ ለማካሄድ ነባራዊ ሁኔታው የማይፈቅድ ስለሆነ በፖለቲካ ምህዳሩና በህዝብ ወሳኝነት ሁሪያ መወያየት አለብን ብለን ፒቲሺን ተፈራርመን ለቦርዱ ያስገባን 33 ፓርቲዎች ጉዳይ ወደ ጎን ተትቶ ቀልድ በሚመስል መልክ በጾታ ጉዳይ ልናወያያችሁ እንፈልጋለን ማለት የህዝብን የምርጫ ባለቤትነት የሚጋፋ ተግባር ሆኖ አግኝተነዋል።” ካሉ በሁዋላ፣ ቦርዱ ጾታን በተመለከተ እና አሁን ላለንበት ሁኔታ ቀላል የሆነ ጉዳይ ጠቅሶ በጠራው የፖለቲካ ፓርቲዎች የውይይት  መድረክ የማንሳተፍ መሆናችንን ፔቲሺን የፈረምን 33 የፖለቲካ ፓርቲዎች እናሳውቃለን።” ብለዋል። 33ቱ የፖለቲካ ድርጅቶች ምርቻ ቦርድ በገለልለተኛ ወገኖች እንዲቋቋም፣ ነጻና ፍትሀዊ የመገናኛ ብዙሀን እንዲኖሩ፣ የመንግስት የመገናኛ ብዙሀን ሁሉንም ድርጅቶች በእኩል እንዲያገለግሉ፣ መከላከያ፣ ፖሊስና የደህንነት ተቋማት በነነጻነት እንዲዋቀሩ፣ በተቃዋሚዎች ላይ የሚደርሰው ማዋከብ እንዲቆም የሚሉና ሌሎችንም በርካታ ጥያቄዎች መጠየቃቸው ይታወሳል።

ፕላምፕኔት የተሰኘውን ምግብ ለገበያ ያቀረቡ የንግድ ተቋማት እርምጃ ተወሰደባቸው

Image
አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 9 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የሃዋሳ ከተማ ጤና መምሪያ የምግብ እጥረት ላጋጠማቸው ህጻናት በነጻ የሚሰጠውን "ፕላምፕኔት" የተሰኘ ምግብ ለገበያ ባቀረቡ 25 የንግድ ተቋማት ላይ ህጋዊ እርምጃ እየወሰደ ነው። ምግቡን መንግስት ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ከፍተኛ ወጪ እያደረገበት ለታለመላቸው ህጻናት እንዲደርስ የሚያደርግ ሲሆን ፥ የሚቀርበውም በጤና ተቋማት በኩል በነጻ እና በባለሙያ ትዕዛዝና ክትትል ብቻም ይሰጣል። ይሁን እንጂ በሃዋሳ ከተማ ይህ ህይወት አድን ምግብ ከታለመለት ዓላማ ውጪ እየዋለ መሆኑን ፥ በመምሪያው የጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶችና ግብዓቶች ስርዓት ቁጥጥር ዋና የስራ ሂደት ባለቤት አቶ ዘመን ለገሰ ተናግረዋል። በተለያዩ መንገዶች ከየጤና ተቋማቱ እየወጣ ለንግድ እየቀረበ በመሆኑ ፥ ዛሬን ጨምሮ ሰሞኑን መምሪያው ይህን ምግብ ለገበያ በሚያቀርቡ የንግድ ተቋማት ላይ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ተገዷል። አቶ ዘመን እንዳሉት ወደ እርምጃ የተገባው በተለያዩ መንገዶች በተደጋጋሚ ፥ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ቢሰጥም ለውጥ ሊመጣ ባለመቻሉ ነው። አስቀድሞ እርምጃ ተወስዶባቸው ዳግም ወደ ህገ ወጥ ስራው ላለመግባት ፥ መተማመኛ ፈርመው የንግድ ተቋሞቻቸው የተከፈቱላቸው እንዳሉም ነው ያስረዱት። በዚህ ህገ ወጥ ስራ ውስጥ ተሳትፈዋል በሚል ተጠርጥረው በፍርድ ሂደት ላይ የሚገኙ ሁለት የህክምና ባለሙያዎችም አሉ ነው ያሉት አተ ዘመን። ከጉዳዩ አሳሳቢነት አንጻር የጤና መምሪያው በከተማዋ የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮን ጨምሮ ፥ ዘጠኝ ያህል ባለድርሻ አካላትን ያካተተ የህብረተሰብ ጤና ተቆጣጣሪ ግብረ ሃይል ማቋቋሙን በዛብህ ማሞ ዘግቧል።

በመጪው ሚያዝያ ለሚካሄደው ምርጫ የምርጫ ቁሳቁሶች ሊከፋፈል ነው

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 5/2005(ዋኢማ)   - በመጪው ሚያዝያ 6 እና 13 ለሚካሄደው የአካባቢና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤቶች ምርጫ የምርጫ ቁሳቁሶችን ከዛሬ ጀምር ማሰራጨት እንደሚጀምር የምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የቦርዱ የህዝብ ግንኙነት ማስተባበሪያ ኃላፊ ወይዘሮ የሺ ፍቃዱ ዛሬ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ ለምርጫው የሚያስፈልጉ የምርጫ ቁሳቁሶችን ቦርዱ በማዘጋጀት በሚቀጥሉት ሁለትና ሶስት ቀናት ለሁሉም ክልሎች ለማሰራጨት ዝግጅቱን አጠናቋል። ቦርዱ ካሁን በፊት የመራጮች መመዝገቢያና የምርጫ ካርዶችን በአማርኛ ብቻ ያሳትም እንደነበረ ጠቁመው፤ በዘንድሮው ምርጫ ግን ከአማርኛው በተጨማሪ  በኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ አፋርኛና ሶማሊኛ ቋንቋዎች ማዘጋጀቱን ገልፀዋል። የዘንድሮው ምርጫ ፍትሀዊነቱ የተረጋገጠ ለማድረግም ለባለድርሻና ለአስፈፃሚ አካላት ስልጠና መሰጠቱን ተናግረው፤ በቅርቡም ከ100 በላይ ለሚሆኑ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ስልጠና እንደሚሰጥ ወይዘሮ የሺ ገልፀዋል። ምርጫውን በእውቀት ላይ የተመሰረተ ለማድረግም በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች በተለያዩ ቋንቋዎች ትምህርት በመሰጠት ላይ መሆኑን ጠቁመዋል። የምርጫ ክልል የምርጫ አስፈፃሚዎችን የመመልመሉ ስራም መጠናቀቁን ጠቁመው፤ በዚህም 2ሺ የሚሆኑ አስፈፃሚዎች በቋንቋቸው ስልጠና እንዲወስዱ ተደርጓል ብለዋል። የምርጫ አስፈፃሚዎች ገለልተኛ እንዲሆኑ ጥረት እየተደረገ ነው ያሉት ወይዘሮ የሺ የስራ ልምድና የትምህርት ዝግጅት እንዲኖራቸው በተለይም የሴቶችና የወጣቶች ተሳትፎ ከባለፈው ምርጫ የተሻለ እንዲሆን ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል። እንደ ወይዘሮ የሺ ገለፃ የመራጮችና የእጩዎች ምዝገባ ቦርዱ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከታህሳስ 22 ጀምሮ እንደሚካሄድ

የመጠለያ እጥረትና የጋራ መኖሪያ ቤት ተስፋ በሐዋሣ

Image
በአስፋው ብርሃኑ ልዩ ዘጋቢ ከሐዋሣ ሐዋሣ ከተማ በ1952 ዓ.ም. ስትቆረቆር የነዋሪዎቿ ቁጥር ከ2,500 አይበልጥም ነበር፡፡ ኀዳር 2003 ዓ.ም. የአምሳኛ ዓመት ልደቷን ስታከብር የሕዝቧ ቁጥር ከሦስት መቶ ሺሕ በላይ የደረሰ ቢሆንም ፈጣን የሕዝብ ቁጥር ዕድገት የተከሰተው ባለፉት አሥር ዓመታት ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ በአገራችን በፍጥነት እያደጉ ከመጡት ከተሞች ግንባር ቀደም የሆነችው ሐዋሣ ዛሬ አራት መቶ ሺሕ ለሚገመት ሕዝቧ መጠለያ እያጠራት ከመሆኑም በላይ “ለመኖሪያ የተመቸች” መባሏን ተከትሎ እንዲሁም የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴዎች መጐልበት በርካታ ዜጐች እንዲፈልሱ አስችሏል፡፡ መሰል ሁኔታ የመኖሪያ ቤት እጥረትንና የአንድ ክፍል ወርሃዊ ኪራይ ንረትን አስከትሏል፡፡ የከተማዋ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት እጥረትን ለመቅረፍ የአገራዊ ፖሊሲ አካል የሆነውን የጋራ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ከ1999 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እያደረገ ቢሆንም እጥረቱና የኪራይ ንረቱ ዛሬም ለሐዋሣ ነዋሪዎች የኑሮ ውድነቱ አካል ሆኗል፡፡  የሕዝብ ቁጥር ዕድገትና የመጠለያ እጥረት  ሐዋሣ የክልሉ መንግሥትና የሲዳማ ዞን አስተዳደር መቀመጫ መሆንዋ፣ የመሠረተ ልማት አውታሮች ግንባታ ፕሮጀክቶች መስፋፋት፣ የንግድና የቢዝነስ እንቅስቃሴዎች መበራከት የግልና የመንግሥት የትምህርት ተቋማት መንሰራፋትና ሌሎች ተያያዥ ነገሮች ለሐዋሣ ለፈጣኑ የሕዝብ ቁጥር ዕድገት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ለቢዝነስ፣ ለትምህርትና ለሥራ ጉዳይ ወደ ሐዋሣ የመጣ ዜጋ ቡና ቤት አይኖርምና ቋሚ መጠለያ ይፈልጋል፡፡ ያለው አማራጭ ከተገኘ የቀበሌ (ዕድለኛ ከሆነ) እና የግለሰብ መኖሪያ ቤት ተከራይቶ መኖር ነው፡፡ ይሁንና በአጭር ጊዜ ውስጥ የአንድ ክፍል ኪራይ ዋጋ አቅም የሌላቸውን በየወሩ ቤት እንዲቀያይሩ እ

Protection of agri-food names in Africa, Sidama Coffee is among 19 covered products

Image
The European Commission signed, on 26 November, in Zanzibar, Tanzania, a cooperation agreement with the African Regional Intellectual Property Organisation (ARIPO) to improve the protection of traditional agricultural products (geographical indications or GIs) in Africa. This will involve, among other matters, promoting the GI legal framework, informing producers and other stakeholders and enhancing the public’s awareness of GIs and their potential for African producers.  The agreement has a non-legally binding status and covers 19 product names: Zanzibar cloves (clous de girofles) from Tanzania, Rift Valley coffee from Tanzania, Sidamo coffee from Ethiopia, Rooibos from South Africa, Karoo lamb from South Africa, Beurre de karité du plateau Massif from Burkina Faso, Miel blanc d’Oku from Cameroon, Poivre blanc de Penja from Cameroon, Shama shea butter from Ghana, Ghana fine flavour cocoa, Café Diama from Guinea, Rwanda mountain coffee, Mount Kenya roses from Kenya, Ngoro Ngoro

Readers chose the D.C. area’s best coffee shop. H Street’s Sidamo which roasts its own beans is among the best

Image
Now that the scientific world is  finally confirming what coffee drinkers always knew  — that it’s okay to drink as much coffee as you like — allegiance to a single purveyor seems like a moot point. Yet as of this writing, nearly 1,000 votes poured in for last week’s reader poll to name  the area’s best coffee shop . The winner? With more than a quarter of the votes, it was  Blind Dog Cafe . The Shaw cubbyhole, which occupies Darnell’s Bar during daytime hours, opened in February and has since won loyalists with its PT’s coffee, warm pimento-cheese-and-egg croissant sandwiches and shabby-chic decor. •  What’s the best coffee shop in the D.C. area? Peregrine Espresso , last year’s winner  Northside Social , and  Tryst  also fared well, along with  Big Bear Cafe  and the new  Kafe Bohem . Though our poll put forth 17 options, including selections from our 2011 list, readers wrote in to name a few favorites they felt were robbed. Among them: Alexandria’s brilli

Bolla Market Brews Up Organic, Fair Trade and Bird Friendly Coffee

Image
Along with daily choices of light and dark roasts, Bolla Market coffees will include quarterly limited-time offerings starting with a pumpkin spice holiday flavor to be followed by single origin coffees such as Guatemala Huehuetenango and Ethiopia Natural Sidamo.  The retailer has become one of the largest convenience store chains to provide only organic, Fair Trade and Bird Friendly shade-grown coffee in the United States. ​NEW YORK CITY – Bolla Market, the New York area’s chain of high-end convenience stores, announced it has switched to only top-quality organic, Fair Trade and Bird Friendly® specialty coffee for all its coffee offerings. Bolla Gourmet Organic Coffee will be sold at the company’s 21 locations recently reopened post-Hurricane Sandy and located from Brooklyn to Riverhead on Long Island,as well as on Staten Island. In making the switch, the company will become one of the largest convenience store chains to provide only organic, Fair Trade, and Bird F

Tree species diversity, topsoil conditions and arbuscular mycorrhizal association in the Sidama traditional agroforestry land use, southern Ethiopia

Image
Zebene ,  Asfaw  (2003).  Tree species diversity, topsoil conditions and  arbuscular   mycorrhizal  association in the Sidama traditional agroforestry land use, southern Ethiopia.  Diss. ( sammanfattning /summary) Uppsala :   Sveriges   lantbruksuniv .,  Acta   Universitatis   agriculturae   Sueciae .  Silvestria , 1401- 6230 ;  263  ISBN 91-576-6347-5  [Doctoral thesis] Abstract Sidama farmers cultivate trees to meet their food, wood, fodder and other service needs. Tree cultivation intensity has increased during the past three decades. Significant positive correlation was found between farm size and number of species, and number of stems per farm. The number of tree species per farm averaged 16 and ranged from 4 to 28. Within farms, about ten different field types were identified of which  enset  fields contain the highest number of species. Wealthy households have more tree species than poor households. In general the largest number of tree species, the large

It is not population growth alone but the Deprivation of opportunities and Deterioration of Human Capital : alarming famine bells in Sidama land.

Mulugeta Daye. Introduction For Malthusian apologists and those incapable leaders to feed their people, Population growth is the main  reason to blame for famine causation. The assumed linkage among famine, starvation, and mass mortality in both popular conceptions and technical definitions stems directly from the debate started by Malthus more than two centuries ago. Yet as more nuanced analyses have recently demonstrated, famine can occur in varying degrees of severity well before critical food shortages become evident. For example, villagers in Sudan distinguish a “famine that kills” from a range of other food crises experienced at the household level that may cause hunger and destitution but not necessarily lead to death (de Waal 2004). This means without creating window of opportunities to human capital building through, education, health facilities, fair job opportunities, population growth may contribute to pressure on available livelihood assets and opportunities

በኢትዮጵያ ''ሃሎ ዶክተር'' የተሰኘ የምክር አገልግሎት መስጫ አገልግሎት ተጀመረ

አዲስ አበባ ታህሳስ 8/2005 በኢትዮጵያ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ ሕሙማን ከሐኪሞች ምክር የሚያገኙበት ''ሃሎ ዶክተር'' የተሰኘ አገልግሎት በይፋ ተጀመረ። አገልግሎቱ በኦሮምኛ፣በትግሪኛና በሶማሊኛ ቋንቋዎች ለመጀመርም ታቅዷል። የቴሌ ሜዲስን የሕክምና አገልግሎት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ዮሐንስ ወዳጄ ዛሬ ለኢ ዜ አ እንዳስታወቁት ለ24 ሰዓት የሚሰጠው አገልግሎት በየትኛውም የአገሪቱ ክፍል ሆነው ምክር የሚፈልጉ ሕሙማንን ለመርዳት ያስችላል። በተጨማሪም ቤታቸው ሆነው የሐኪም ድጋፍ የሚፈልጉ ሕሙማንን እንደሚያግዝም አስረድተዋል። እንዲሁም በሕመም ወይም በአደጋ ለተጎዱ ሰዎች የአምቡላንስ አገልግሎት በማቀናጀት እገዛ እንደሚያደርግ ዶክተር ዮሐንስ አስታውቀዋል። ''ሕሙማን ካሉበት ሆነው በሞባይል ስልካቸው አማካይነት ወደ 8896 መደወል የሐኪም ምክር ሲጠይቁ በመሥመር ላይ ያለው ሐኪም ከሕመማቸው እንዲፈወሱ ተገቢውን ምክር በመስጠት ይረዳቸዋል።ለዚህም ከስልካቸው ሂሳብ ተቀናሽ የሚሆን መጠነኛ ሂሳብ ይቆረጣል'' ሲሉም አብራርተዋል። በአገሪቱ የሞባይል አገልግሎት መስፋፋትና የወደፊት አቅጣጫው አገልግሎቱን ለማስጀመር ጥሩ መሠረት እንደሆነም ዋና ሥራ አስኪያጁ አመልክተዋል። አገልግሎቱ ለጊዜው በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች በ10 ሐኪሞች መጀመሩንም ተናግረዋል።በያዝነው ዓመትም የሐኪሞቹን ቁጥር ወደ 50 ለማሳደግ መታቀዱን ገልጸዋል። አገልግሎቱን በኦሮምኛ፣በትግሪኛና በሶማሊኛ ቋንቋዎች ለመጀመርም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል። አገልግሎቱ ቀደም ሲል በአውሮፓና በአሜሪካ፣በቅርቡ ደግሞ በደቡብ ምሥራቅ አገሮችና በላቲን አሜሪካ እንዲሁም በአፍሪካ እየተስፋፋ መምጣቱን ዶክተር ዮሐን

የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ፈተናዎችና የሦስቱ ተዋንያን ሚና ሲገመገም

Image
በጋዜጣው ሪፖርተር የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት  በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ የጀመረውን ውይይት ኅዳር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስቀጥሎ ነበር፡፡ በተጠቀሰው ቀን ያካሄደው የውይይት ርዕስ ‹‹ወቅታዊው የአገራችን የፖለቲካ ሁኔታና የፖለቲካ ፓርቲዎች የመሰባሰብ ሚና›› የሚል ነበር፡፡ በዚህ ውይይት ላይ የፓርቲው የፖለቲካ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሙላቱ ጣሰው ለፓርቲው አባላት የመወያያ ጽሑፍ አቅርበዋል፡፡ እሳቸው በኢትዮጵያ ሁሉም ዓይነት የዜጎች መብቶች የሚከበሩበትና ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል የሚኖርበት ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት፣ ባለፉት ዓመታት በተከታታይ የተደረጉት ጥረቶች ሁሉ ውጤት አላመጣም ይላሉ፡፡ በውይይቱ ላይ እነዚህ ሁሉ ጥረቶች ለምን ለውጥ እንዳላመጡ አቶ ሙላቱ ሲያብራሩ፣ ሦስት ተዋናዮችን በተወሰነ ደረጃ መመልከት አስፈላጊ መሆኑን በመጠቆም ማስረዳታቸውን ቀጠሉ፡፡ ሦስቱ ተዋንያን የተባሉት ገዥው ፓርቲ፣ ተቃዋሚዎችና ሕዝብ ናቸው፡፡ ገዥው ፓርቲ ገዥውን ፓርቲ (ኢሕአዴግ) ከትናንት እስከ ዛሬ ብለው አጠር አድርገው በተነተኑበት ክፍል የራሱን አገር አስገንጥሎ ዕውቅና የሰጠ፣ የአገሪቱን የባህር በር የዘጋ፣ የአገሪቱን ሉዓላዊነት ጥያቄ ውስጥ ያስገባ፣ የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅሞች አሳልፎ የሰጠና ፍትሐዊ የሀብት ክፍል የሌለበት አምባገነናዊ ሥርዓት ማስፈኑን፣ በጦርነት ወቅት የወረሳቸውን ንብረቶችና ሀብቶች በእጁ ይዞ የፓርቲ ኩባንያዎችን እያስፋፋ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ‹‹የገዥው ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የአገሪቱን ሀብት በመቆጣጠር ላይ ናቸው፡፡ አገራችን ከበቂ በላይ ለም መሬትና ዓመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞች እያሏት፣ በምግብ ሰብል ራሳችንን ባለመቻላችን ሕዝባችን ለከፍተኛ ረሃብ ተዳርጓል፤›› ያሉት አቶ ሙላቱ