Posts

‹‹ሐዋሳ ላንጋኖ ለሽርሽር ……

በሔኖክ ረታ ኅዳር መባቻ ማለዳ ላይ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ ቅጥር ግቢ ውስጥ የተሰበሰበው የሚዲያና ኮምዩኒኬሽን ሴንተር (ኤምሲሲ) ሠራተኛ በድርጅቱ አማካይነት የተሰናዳለትን የሽርሽር ጉዞ ለመጀመር በንቃት ቦታ ቦታውን ይዟል፡፡ ሁለተኛውን የሚዲያና የኪነጥበብ ባለሞያዎች የእግር ኳስ የዋንጫ ውድድርን በሦስተኛነት በማጠናቀቁ ነበር ከሌሎቹ አሸናፊዎች ጋር በመሆን ይህን የጉዞ ዕድል ያገኘው፡፡ ከማለዳው አንድ ሰዓት ላይ ወደ ሐዋሳ ከተማ የተጀመረው ጉዞ ከአዲስ አበባ በስተምሥራቅ 30 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ዱከም ከተማ ላይ የቁርስ ቆይታ ነበረው፡፡ በቀድሞው አትሌት ወርቁ ቢቂላ ሆቴል ቁርስ የተመገቡት የኤምሲሲ አባላት ከቀድሞው አትሌት ጋር ትውውቅና የተወሰነ ቆይታ የማድረግ አጋጣሚም ነበራቸው፡፡ ቢሾፍቱንና ሞጆን በተከታታይ አልፎ በግምት አምስት ሰዓት ገደማ ላይ የካስቴል ወይን እርሻና ፋብሪካ ለመጎብኘት አዳሚ ቱሉ ወረዳ ደርሷል፡፡ በዘመናዊ ማሽኖችና ቴክኖሎጂዎች የተገነባው የወይን መጥመቂያ ፋብሪካ ከተንጣለለው የወይን እርሻ በሰው ኃይል አማካይነት የተለቀመውን ፍሬ በረዥም የጊዜ ሒደት ውስጥ የሚፈለገውን የወይን ጣዕም አቀነባብሮ ለገበያ የሚያቀርብ ግዙፍ የወይን እርሻና ማምረቻ እንደሆነ በድርጅቱ የምርት ክፍል ባለሞያ የሆኑት አቶ ዳዊት ገብሬ ለጎብኚዎቹ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡ እንደ ብረት ምጣድ በጋለው የመኪናው ጣራና ግድግዳ በኩል እየገባ የሚፋጀው ጠራራ ፀሐይ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ሙቀት ቢፈትንም በጨዋታና በሙዚቃ የተዋዛውን ጉዞ ሊያደበዝዘው አልቻለም ነበር፡፡ መቂ፣ ዝዋይንና አርሲ ነገሌ ከተሞችን በፈታኝ የፀሐይ ሙቀት የጨረሰው ጉዞ ሰባት ሰዓት ገደማ ላይ ከመዳረሻዋ የሐዋሳ ከተማ በ23 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ብቻ ቀደም ብላ የምትገኘውን ሞቅ ያለች

ግልጽነትና ተጠያቂነት የመልካም አስተዳደር ወሳኝ መሣሪያዎች ናቸው

Image
ሕዝብም መልካም አስተዳደር እፈልጋለሁ ይላል፡፡ መንግሥትም መልካም አስተዳደርን ማስፈንና ማረጋገጥ ራዕዬ፣ ዓላማዬና ዕቅዴ ነው ይላል፡፡ በዚህ ላይ ልዩነት የለም፡፡ በአባባል፣  በፍላጎትና በምኞት ደረጃ፡፡ መልካም አስተዳደርን ተግባራዊ ለማድረግ ግን የግድ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን በተግባር ማስፈን ያስፈልጋል፡፡ ግልጽነትና ተጠያቂነት ከሌለ መልካም አስተዳደር አይኖርም፣ አይሰፍንም፡፡ ግልጽነት ሲባል ትርጉሙ ‹‹ግልጽና ግልጽ›› ነው፡፡ በሕዝብ ተመርጫለሁ የሚል መንግሥት ውክልና ሰጥቶ፣ መርጦ ለሥልጣን ላበቃው ሕዝብ የሚሠራውንና የሚያስበውን በግልጽ ማሳወቅ አለበት፡፡ ሕዝብ መንግሥትን እዚህ ጋ ተሳስተሃል፣ እዚህ ጋ አጥፍተሃል፣ እዚህ ጋ ጥሩ ሠርተሃል፣ እዚህ ጋ እንዲህ ብታደርግ ይሻላል በማለት ሕገ መንግሥቱ የሰጠውን መብት ተጠቅሞ ሐሳብ ለመስጠት፣ ሂስ ለማቅረብና ድጋፉን ለመግለጽ መንግሥት የሚያከናውነውን ሁሉ በግልጽ ሊያውቀው ይገባል፡፡ መንግሥት ግልጽ ሊሆንለት ይገባል፡፡ ሕገ መንግሥታችን ግልጽነትን ይደግፋል፡፡ ሁሉም ነገር ለሕዝብ ግልጽ እንዲሆን የሚያዝና የሚደነግግ ሕግም አለን፡፡ የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነፃነት አዋጅ፡፡ በሕገ መንግሥትና በሕግ በኩል በአገራችን ግልጽነት እንዳይኖር የሚያደርግ አንዳችም ነገር የለም፡፡ በተግባር ግን ግልጽነት እየተዳከመ ነው፡፡ በተግባር ግን ቢሮክራሲው የሚጠቅመውን ይናገራል፤ የማይጠቅመውንና የሚያጋልጠውን ይደብቃል እንጂ ግልጽነት (ትራንስፓረንሲ) እውን ሊሆን አልቻለም፡፡ ለመልካም አስተዳደር ትልቅ የተደቀነ እንቅፋት የሆነው የግልጽነት አለመኖር ሆኗል፡፡ ተጠያቂነትን (አካውንተቢሊቲ) በሚመለከትም ሕገ መንግሥታችንና ሕጎቻችን የሚደግፉትና የሚያበረታቱት ናቸው፡፡ በተግባር ግን ተጠያቂነት እየጠፋ ነው፡፡ ቢሮክራ

Media and the political process

The thinking that media and the political process have a dialectical relationship, that includes action and reaction, is a recent and not yet well developed theory of mass communication. Whether media actually does have the ability to influence foreign policy is the subject of intense debate among scholars, journalists and policy makers.  “The CNN (Cable News Network) Effect” , as it is called by scholars, however, demonstrates the impact of new global real time media. The CNN effect regards the role of media as typically substantial if not profound. Some radicals even define the CNN effect as a loss of policy control on the part of policymakers, because of the power of the media; a power that they can do nothing about. Their thinking is a major deviation from the existing and almost hegemonic thinking of the propaganda model. According to propaganda model the relationship between the media and the political process was seen as a rather supplementary one. The media were thought to

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ውስጥ - የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽኗ እና የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ

Image
በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት መመረጥ ላይ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነሯ እና የሰመጉ ዳይሬክተር ለቪኦኤ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ​​ የኢትዮጵያ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባልነት መመረጥ ካስመዘገበቻቸው የምጣኔ ኃብት እና ማኅበራዊ ስኬቶች በአካባቢውና በምክር ቤቱ ምሥረታ ላይም ከተጫወተቻቸው ሚናዎቿ ጋር የተያያዙ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር አምባሣደር ጥሩነህ ዜና አስታውቀዋል፡፡ የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ​​ በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫው በወቅቱ ያስደነገጠው መሆኑንና ምናልባትም ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች አያያዟን እንድታሻሽል ግፊት ማሣደሪያ አጋጣሚ ሊሆንም እንደሚችል የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ዋና ዳይሬክተር አቶ እንዳልካቸው ሞላ አመልክተዋል፡፡ ዝርዝሩን ከዘገባው ያዳምጡ፡፡ ዝርዝሩን ከዘገባው

የመልካም አስተዳደር ችግር -ያልተሻገርነው የዕድገት ማነቆ

ብሩክታይት ፀጋዬ በእኛ ሀገር በአንድ ወቅት ደመቅ በሌላ ጊዜ ደግሞ ድብዝዝ የሚሉ ጉዳዮች በርካታ ናቸው፡፡ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ስለተናገሩትና በመገናኛ ብዙሃን ስለ ተቀባበሉት ብቻ ሞቅ የሚሉ ጉዳዮች በርካታ ናቸው፡፡ አንዳንዴ ሞቅታው በቃላት ብቻ ሳይሆን በተግባርም ይገለጻል፡፡ ከእነዚህ አንድ ወቅት ያዝ ሌላ ጊዜ ደግሞ ለቀቅ ከምናደርጋቸው ብዙ ጉዳዮች አንዱ የመልካም አስተዳደር ጉዳይ ነው፡፡ በአንድ ወቅት ስለ መልካም አስተዳደር ብዙ ብዙ ተባለ፡፡ በእርግጥ ይህ ጊዜ ማን አገልጋይ ማን ደግሞ ተገልጋይ እንደሆነ ጥርት ያለ ግንዛቤ የተያዘበትና በመልካም አስተዳደር ረገድ አንድ ወሳኝ ምዕራፍ የተሸጋገርንበት በመሆኑ ጉዳዩ መነሳቱ በራሱ መልካም ነገር ነው ማለት ይቻላል፡፡ ጉዳዩ በመነሳቱ «ደንበኛ ንጉሥ ነው» አመለካከትን ለማዳበርም ተችሎ ነበር፡፡ የዛሬን አያድ ርገውና፡፡ «የት መሄድ ይፈልጋሉ?»ከሚለው አቅጣጫ ጠቋሚ ጀምሮ የሠራተኞችን ስም በየቢሮው በር ላይ መለጠፍና ባጅ እንዲያን ጠለጥሉ እስከማድረግ፣የቅሬታ ሰሚ አካላት በማቋቋም ተጠያቂነት ያለው አሠራር እስከማስፈን እሰየው የሚያሰኙ በጐ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ከዓመታት በፊት የተተከሉት የአስተሳሰብና የአሠራር ሥርዓቶች አሁንም ቀጥለውና ተጠናክረው የሚተገበሩባቸው ተቋማት እንዳሉ ሁሉ እነዚህ የሕዝብ አገል ጋይነት መገለጫዎች ለሙሰኞችና ለመልካም አስተዳደር ጠንቆች ሽፋን ሲሰጡም ተመል ክተናል፡፡ ተጠቃሚዎችን በአግባቡ ማስተናገድ ዓላማቸው አድርገው ከሚንቀሳቀሱ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ዓይነት ተቋማት እንዳሉ ሁሉ አንዴ መልካም ሌላ ጊዜ ደካማ አፈፃፀም እያሳዩ በአንድ ወቅት ደመቅ ብለው ሌላ ጊዜ ደግሞ ሸርተት ሲሉ የምናያቸው ተቋማትም መኖራቸው የማይካድ ነው፡፡ ሌሎቹ ደግሞ የ

የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ በኦሮሚያና በደቡብ ክልሎች በ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ የርብና ጊዳቦ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እያካሄደ መሆኑን ገለጸ።

Image
አዲስ አበባ ህዳር 09/2005 የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ በኦሮሚያና በደቡብ ክልሎች በ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ የርብና ጊዳቦ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እያካሄደ መሆኑን ገለጸ። ግንባታው ሲጠናቀቅ 26 ሺህ ሄክታር የሚደርስ የመስኖ መሬትን ማልማት እንደሚያስችል ተገልጿል። የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ አስተማማኝ የውኃ አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል የርብና የጊዳቦ መስኖ ልማት ፕሮጀክቶች የግድብ ግንባታ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በደቡብ ጎንደር ዞን በእብናትና ፋርጣ ወረዳዎች እንዲሁም በፎገራ ሜዳማ አካባቢ የሚገነባው የርብ ግድብ 234 ሜትር ኩብ ውኃ የመያዝ አቅም እንዳለው ገልጸዋል፡፡ የግድቡ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ 14 ሺህ ሄክታር መሬት በመስኖ የማልማት አቅም የሚኖረው ሲሆን ከ28 ሺህ በላይ አባዎራዎቸን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ በግድቡ ግንባታ ወቅት 400 ለሚደርሱ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር የታቸለ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 75 ያህሉ ሴቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። የርብ ግድብ ግንባታ አጠቃላይ ወጪ 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ የግድቡ ግንባታ በያዝነው ዓመት ሰኔ ወር እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋዕል፡፡ በተመሳሳይም በኦሮሚያና በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች ክልሎች በሲዳማና ቦረና ዞን አዋሳኝ በሚገኙ ዓባያና ለኮዓባያ ወረዳዎች 117 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ የመያዝ አቅም ያለው የጊዳቦ የመስኖ ልማት ግድብ ፕሮጀክት በመገንባት ላይ እንደሚገኝ አቶ ብዙነህ አመልክተዋል፡፡ የግድቡ ግንባታ ሲጠናቀቅ 11 ሺህ 924 ሄክታር ማልማት የሚያስችል ሲሆን ከ79 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍልን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አስረ

የመጀመርያው የቡና ሙዚየም በመጠናቀቅ ላይ ነው

Image
በዮናስ አብይ በኢትዮጵያ የመጀመርያው ነው የተባለለትና ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ በደቡብ ክልል በቦንጋ ከተማ በመገንባት ላይ የሚገኘው ብሔራዊ የቡና ሙዚየም በቅርቡ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር የቦንጋ ዞን አስተዳደር አስታወቀ፡፡ ለ2000 ዓ.ም. የሚሊኒየም በዓል ተቋቁሞ የነበረው የበዓሉ አስተባባሪ ሴክሬተሪያት ሥራው ከመጠናቀቁ በፊት ካሳለፋቸው ውሳኔዎች አንዱ፣ የቡናን ባህላዊና ታሪካዊ አመጣጥ የሚያሳይ ሙዚየም ስለመገንባት ነበር፡፡ ምንም እንኳ የሙዚየሙ ግንባታ ከዕቅዱ ቢዘገይም በጥቂት ወራት ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚጀምር የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ክፍሌ ገብረ ማርያም በተለይ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ እንደ አስተዳዳሪው ገለጻ፣ የሚሊኒየም አካባበር አስተባባሪ ኮሚቴው በወቅቱ ኃላፊነቱን ለደቡብ ክልል የሰጠ ቢሆንም፣ ክልሉ ደግሞ ግንባታውን የማስተባበርና የመከታተል ኃላፊነቱን ለዞኑ አስተዳደር ሰጥቷል፡፡ ሙዚየሙ ብሔራዊ እንዲሆን በመወሰኑ በጀቱን የፌዴራል መንግሥት እንዲመድብ በቅድሚያ ተወስኖ የነበረ ቢሆንም፣ በኋላ ግን ክልሉና ዞኑ እንዲሸፍኑ መደረጉን አክለው ገልጸዋል፡፡ ግንባታው ለምን እንደዘገየ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ክፍሌ በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹በወቅቱ የሚያስፈልገንን ያህል በጀት ማግኘት ባለመቻላችንና የግንባታ ዕቃ ባለማሟላታችን ነበር፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡ ሙዚየሙ ቋሚና ጊዜያዊ ኤግዚቢሽኖችን የሚያካትት ሲሆን፣ የዲዛይን ሥራው የገጠሪቱን ኢትዮጵያ ባህላዊ ቤቶችን እንዲያንፀባርቅ ተደርጐ የተሠራ ነው፡፡ በተጨማሪም ሙዚየሙ የአገሪቷን የቡና መገኛነት ከማንፀባረቁም ባሻገር የቡናን ባህላዊና ታሪካዊ ዳራና ሥነ ሥርዓት እንዲያሳይ ታስቦበት የተሠራ መሆኑን የዞኑ አስተዳዳሪ ያብራራሉ፡፡ ግንባታውን ታዬ አስፋው

የኢትዮጵያ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ወደ ግብፅ ሊጓዙ ነው

Image
በዮሐንስ አንበርብር ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ አባላትን ያካተተ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥትን በመወከል፣ ኢትዮጵያ የምትገነባው ታላቁ የህዳሴ ግድብ በዓባይ ወንዝ ላይ ምንም ጉዳት የሚያስከትል መሆኑን ለማስረዳት፣ የኢትዮጵያንና የግብፅን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከር የሚል ተልዕኮ ይዞ ወደ ግብፅ ሊያቀና ነው፡፡ የዲፕሎማሲ ቡድኑ አባላት ከዩኒቨርሲቲ ምሁራን፣ ከታዋቂ ሰዎች፣ ከመገናኛ ብዙኅን፣ ከሥነ ጥበብና ከእምነት መሪዎች የተውጣጡ ሲሆን፣ በትናንትናው ዕለትም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተገኝተው በተጠባባቂ ማኒስትሩ አምባሳደር ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ ገለጻ ተደርጐላቸዋል፡፡ ኢትዮጵያና ግብፅ የረዥም ዘመናት ግንኙነት ያላቸው አገሮች መሆናቸውን በመጥቀስ ገለጻቸውን የጀመሩት ተጠባባቂ ሚኒስትሩ፣ ይህ ግንኙነታቸው ከተፈጥሮና ከመንፈሳዊ እምነት ጋር የተዛመደ እንደሆነ አስታውሰዋል፡፡ በዚህ ረጅም ዘመን የሁለቱን አገሮች ግንኙነት የሚያስተሳስሩ በርካታ መልካም ነገሮች የመኖራቸውን ያህል፣ በተለያዩ ጊዜያት የተከሰቱ የፖለቲካ መሪዎችም ግንኙነታቸውን ሲያሻክሩና ጠባሳ ለመፍጠር ሲሞክሩ እንደነበር አስረድተዋል፡፡ ኢሕአዴግ ሥልጣን ከያዘ በኋላ ግን ሁለቱ አገሮች ከዚህ ቀደም የነበራቸውን አለመግባባት ለመቅረፍ ጥረት መደረጉን የገለጹት ተጠባባቂ ሚኒስትሩ አምባሳደር ብርሃነ፣ እ.ኤ.አ. በ1993 የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ወደ ግብፅ በመሄድ የሥራ ጉብኝት ያደረጉ መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ በዚህ ወቅትም አቶ መለስ መንግሥታቸው በዓባይ ጉዳይ ላይ መወያየትን እንደሚፈልግ በመግለጻቸው፣ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የሁለቱ አገሮች ውይይት እንደተጀመረና በከፍተኛ ሁኔታ እንዳደገ ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ግብፆች ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ

Teddy’s “journey to love” Awassa Concert Full Report

Image
By Tibebeselassie Tigabu For many fans of Teddy Afro, traveling 277 km to Hawassa (Awassa) was not too much. Rather, it is a distance that they can travel easily to see and support the artist they love. It is not only from Addis Ababa that the fans of Teddy Afro went to Awassa. Folks from Moyale and Dilla were also at the concert. There are fans who drove their own cars but there are also those who travelled miles by using public transport to hear him live and to see their beloved artist on stage. On November 3, Awassa was different, bedecked with many posters and fliers of the concert. Especially at the gate of Haile Resort, a humongous poster of Teddy Afro in a white suit was posted. The whole town felt the vibe of the concert. Since it is the second concert after the release of the album, many were still waiting eagerly to see him live. The concert was held in the stadium and even before reaching the stadium the music welcomed people and attracted passersby. Around the

በኢትዮጵያ የከተሞች በዓል ላይ የሃዋሳ ከተማ ተሳትፎ

Image
ከተሞች ተሞክሯቸውን እየተለዋወጡ ናቸው   ዜና ሐተታ አዳማ እንግዶቿን ማስተናገድ ከጀመረች ቀናትን አስቆጥራለች። ማዕዷን እያቋደሰች የምትገኘዋ አዳማ ገፅታዋን ለማስተዋወቅ የአራተኛው የከተሞች ሣምንት ኤግዚቢሽን ተሣታፊ ነች። ለሰባት ተከታታይ ቀናት ለሕዝብ ክፍት ሆኖ የቆየው ኤግዚቢሽን 136 ያህል ከተሞች ወደ አዳማ ያመጣቸውን መገለጫዎቻቸውን በድንኳን በድንኳን ሆነው ራሳቸውን እያስተዋወቁ ናቸው። የአዳማና ዙሪያዋ ከተሞች በርካታ ነዋሪዎች ኢግዜቢሽኑን ይጐበኛሉ። ነዋሪዎቹ አዳማ በዘንድሮው የከተሞች ውድድር አንደኛ እንደምትወጣ ይገልፃሉ። የከተማዋን ገፅታ በኤግዚቢሽኑ እያስጎበኙ የሚገኙ አካላትም ይህንኑ ያጠናክራሉ። አቶ ዘላለም አስራት የአዳማ ከተማን ገፅታ ለማሳየት በተዘጋጀው ድንኳን ውስጥ ስለቀረቡት የተለያዩ ዝግጅቶች ሲያብራሩ «የአዳማ ከተማን ማስተዋወቅ ያስፈለገው ከከተሞች ሁሉ በመሪነት ቦታ ላይ እንድትቀመጥ ታስቦ ነው» ይላሉ። እንደ አቶ ዘላለም ማብራሪያ፤ የአዳማ ከተማ ከ63 ሺ በላይ አባላትን ያቀፉ ከ4ሺ 73 በላይ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አሏት። ከ280 ኪሎ ሜትር በላይ መንገዷ በአስፋልትና በኮብልስቶን ተሸፍኗል። ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል የሚያንቀሳቀሱ ከ700 በላይ ባለሀብቶች ይገኙባታል። አዳማ በቀን 45 ሺ የሚሆኑ ሕዝብ ገብቶ የሚወጣበት 7ሺ ያህል ሰዎች ደግሞ የሚያድሩባት ናት። 8ሺና ከዛ በላይ እንግዶችን ሊያስተናግዱ የሚችሉ የተለያዩ የስብሰባ ማዕከላት ያሏት ስትሆን። ይህም ከተማዋን የኮንፈረንስ ከተማ አሰኝቷታል። ለኢንዱስትሪ፣ ለአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ ለሪልስቴት፣ ለጤና፣ ለትምህርትና ለተለያዩ ዘርፎች የሚውል 128ነጥብ 70 ሔክታር መሬት ለልማት ማዘጋጀቷንም አቶ ዘላለም ይጠቁማሉ።  የ

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ከተሞች የህዳሴ ጉዞ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ እንደሚገኝ ገለፁ

Image
“ከተሞች የኢንዱስትሪያሊስቶች መፍለቂያ ማዕከል በመሆን የመለስን ራዕይ ያሳካሉ” በሚል መርህ በአዳማ ሲካሄድ የቆየው 4ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ሳምንት ተጠናቋል፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የትምህርት ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን በዓሉ በከተሞች መካከል የልምድ ልውውጥ ለማድረግ የሚያስችል እና ጠንካሮችን በማበረታታት በዘርፉ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ንቅናቄ መፍጠር የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ የከተሞች የህዳሴ ጉዞ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ ይገኛል ያሉት አቶ ደመቀ በማደግ ላዩ ያሉ ከተሞችን ወደ ላቀ የልማት ደረጃ ለማሸጋገር ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሊረባረቡ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በገጠር እየተመዘገበ ያለው የልማት ውጤት በከተሞች እየታየ ላለው መጠነ ሰፊ ለውጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል ብለዋል፡፡ ከተሞችንና ገጠሮችን አስተሳስሮ መሄድ ቀጣይ የመንግስት አቅጣጫ መሆኑንም ነው አቶ ደመቀ የተናገሩት፡፡ በ4ኛው የከተሞች ሳምንት ለሰባት ቀናት በቆየው ኤግዚቢሽን ላይ በተለያዩ የከተማ ልማት መስኮች ያከናወኗቸውን ተግባራት እና እራሳቸውን በማስተዋወቅ ከየምድባቸው ላቅ ያለ አፈፃፃም ያስመዘገቡ ከተሞች ተሸልመዋል፡፡ በተለይም በስድስት ቁልፍ የከተማ ልማት ስራዎች የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮችም በ4ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ሳምንት ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስራዎች የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል፣ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የትግራይ ክልል ከአንድ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ሲይዙ በመሬት ልማትና ማኔጅመንት ስራዎች ደግሞ የትግራይ ክልል አንደኛ፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ሁለተኛ እና የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አሸናፊ ሆነዋል፡፡

የሲዳማ ሕዝቦች አርነት ንቅናቄን ጨምሮ የዘንድሮ ምርጫ ተቃዋሚ ፓርቲዎችንና ምርጫ ቦርድን ማወዛገብ ጀመረ

በታምሩ ጽጌ በሚያዝያ ወር 2005 ዓ.ም. የሚደረገው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤትና የአካባቢ ምርጫ ከወዲሁ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድንና የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማወዛገብ ጀመረ፡፡ ቦርዱ ጥቅምት 15 ቀን 2005 ዓ.ም. “የምርጫ ሰሌዳ የምክክር መድረክ” በሚል በአዳማ ከተማ በተደረገው ውይይት፣ በወቅቱ ከተሳተፉት 66 የፖለቲካ ፓርቲዎች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት፣ ቦርዱ ካዘጋጀው የመወያያ ርዕሰ ጉዳይ ውጭ የተለያዩ ጥያቄዎችን ማንሳታቸውንና ምላሽ ማጣታቸውን ተከትሎ አለመግባባት ተፈጥሯል፡፡  ቦርዱ ከምርጫ ሰሌዳው በኋላ በሚወጡ የምርጫ የማስፈጸሚያ ደንቦችና መመርያዎችን ረቂቅ አዘጋጅቶ ፓርቲዎቹን ለማወያየት በጠራው የውይይት መድረክ ላይ፣ 41 የሚሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተስማሙበትንና መስተካከል እንዳለበት ያመኑበትን ጥያቄ ማቅረባቸውን፣ በ34 ፓርቲዎች የተወከለውና ሰባት አባላት ያሉት ጊዜያዊ ኮሚቴ ጥቅምት 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስታውቋል፡፡  “በምርጫ ሰሌዳ ዙርያ ከመወያየታችን በፊት የአገሪቱ የፖለቲካ ምኅዳር መጥበብና የምርጫ ውድድር ሜዳው የተስተካከለ አለመሆን፣ ቀደም ብሎ የተደረጉ ምርጫዎች በአፈጻጸም ችግሮች የተተበተቡ መሆቸውን፣ በየደረጃው ያሉ የምርጫ ቦርድ አመራርና አስፈጻሚዎች ተዓማኒነትና ተቀባይነት ላይ ቅድሚያ ሰጥተን ብንወያይ ይገባል፤” የሚል ጥያቄ ከኢሕአዴግና አጋር የፖለቲካ ድርጅቶች ውጭ ያሉት 41 የፖለቲካ ፓርቲ ድርጅቶች ጥያቄ ማንሳታቸውን ኮሚቴው አስታውሷል፡፡  አንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲ፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት፣ ሰማያዊ ፓርቲ፣ የጌዴኦ ሕዝቦች ንቅናቄ፣ የከንባታ ሕዝቦች ኮንግረንስ፣ የሲዳማ ሕዝቦች አርነት ንቅናቄን ጨምሮ 34 የፖለቲካ ፓርቲዎች ከላይ ያነሷቸው ጥያቄዎች

በሲዳማ ዞን 25 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ይካሄዳል

Image
አዋሳ ህዳር 6/2005 በሲዳማ ዞን የሚሊኒየሙን የልማት ግብ ለማሳካት በበጀት ዓመቱ ከ89 ሚልዮን ብር በሚበልጥ በጀት 25 የመጠጥ ውሃ ፐሮጀክት ግንባታ እንደሚካሄድ የዞኑ ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ገለጸ፡፡ የመምሪያው ሃላፊ አቶ አብሩ ዳቃሞ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ከፕሮጀክቶቹ መካከል 20ዎቹ ጥልቅ ጉድጓድ ቁፋሮ ቀሪዎቹ ማከፋፈያ፣ የማጠራቀሚያ ጋን፣ የውሃ ቦኖና ምንጭ ማጎልበት ናቸው፡፡ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶቹ የሚሰሩት በመንግስት፣ በዋሽ፣ በዩኒሴፍ ፕሮግራምና በህብረተሰብ ተሳተፎ መሆኑን ጠቁመው ወደ ስራ ለመግባት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቀዋል፡፡ ፕሮጀክቶቹ በተያዘው የበጀት ዓመት መጨረሻ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀው አገልገሎት እንዲሰጡ ከዞን ምክር ቤት ጀምሮ በየደረጃው ለሚገኙ አመራር አካላትና ህብረተሰብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት መስጠቱን ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ ከ380ሺህ የሚበልጡ የዞኑ ነዋሪዎች የመጠጥ ውሃ አገልግሎት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ሃላፊው ጠቁመዋል፡፡ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶቹ በዞኑ 50 በመቶ ላይ የነበረውን አጠቃላይ የዞኑን የመጠጥ ውሃ ሽፋን ወደ 62 በመቶ እንደሚያሳድግ ገልጸዋል፡፡ በዞኑ ወረዳዎች በሚገኙ 32 ቀበሌዎች ለ2006 የበጀት ዓመት ከመንግስት በተመደበ 75 ሺህ ብር 312 ፕሮጀክቶች ጥናትና ዲዛይን ስራ 24 ተቋማት የጣራ ላይ ውሃ ማሰባሰብ፣ 2ሺህ ነባር ተቋማትን መልሶ የማደራጀት ስራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡ የቦርቻ፣ አለታ ወንዶና አለታ ጩኮ ወረዳ ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት መጠጥ ውሃ ፍለጋ ረጅም ርቀት በመጓዝ ያባክኑት የነበረውን ጊዜ ለልማት በማዋል ምርትና ምርታማነታቸውን ለመጨመር እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡ በ2004 በዞኑ አስራ ሁለት ወ

የሁለት ብሄሮችን ግጭት ማስተዳደር አቅቶኛል ያሉ ሰውዬ በየትኛው ቀመር የ80 ብሄሮች ቀንበር ይሸከማሉ ???

ጥቅምት 10 2005 ዓ.ም. ለንባብ የበቃው የሪፖርተር ጋዜጣ ልዩ ዕትም ለአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ የኋላ ታሪክ ሰፊ ሽፋን ሰጥቶ ብቅ ማለቱ ይታወሳል፡፡ የዘገባውን ተኣማኒነት ለማጎልበት ጋዜጣው የጠቅላይ ሚኒስትሩን የቀድሞ የሥራ ባልደረቦችንና ወዳጆች አግኝቶ ለማነጋገር ብዙ የደከመ ይመስላል፡፡  ሆኖም ግን ሪፖርተር ጋዜጣ የአቶ ኃይለማሪያምን ጠንካራ ጎን ለመዳሰስ ባደረገው ጥረት፤የጠቅላይ ሚኒስትሩን የመጠቅለል ብቃትን በጥርጣሬ ዓይን የሚያዩ  ወገኖች በግብዓትነት ሊጠቀሙበት የሚችሉትን መረጃዎችን ሳያቀብል አልቀረም፡፡  በእኔ እምነት ዘገባው አንባቢያን ዘንድ ሲደርስ በአዘጋጆቹ ዘንድ ፈጽሞ ያልተጠበቀን ትርጉም (unintended interpretation) የመስጠት አቅም አለው፡፡ ለምሳሌ አንዳንድ ወገኖች የአቶ ኃይለማሪያምን ከደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደርነት ወደ ቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ቤተመንግስት ለመዛወራቸው በመንስኤነት የሚያስቀምጡት የአመራር ብቃታቸውን ማነስ ነው፡፡  ሪፖርተር ጋዜጣም ይህንኑ ግምት የሚያጠናክር መረጃን ነበር ይዞ ብቅ ያለው፡፡ የአቶ ኃይለማሪያም የእምነት ተምሳሌትና አማካሪ (Informal adviser) የነበሩ ቢሾፕ ሕዝቅኤል የሲዳማና የወላይታ ግጭት የአቶ ኃይለማሪያም አመራርን ክፉኛ ተፈታትኖት እንደነበረ በጋዜጣው ላይ በግልጽ ተናግረዋል፡፡  ጋዜጣው የቢሾፑን ምላሽ ያስቀመጠው እንደዚህ ነው፦ “አንድ ጊዜ በዚህ በሐዋሳ ጉዳይ አሁን አስቸጋሪውን ጉዳይ ለመወጣት እየሞከርኩ ነው ያለሁትና ጸልዩልኝ ብሎኝ ነበር፤የሚሉት ቢሾፑ አቶ ኃይለማሪያም እንዴት ከክልል ወደ ፌደራል መንግስት በአቶ መለስ ዜናዊ ጥሪ መሠረት እንደሄዱ ያብራራሉ…..” በዚህ ጉዳይ ላይ በጣ