Posts

የሲዳማ ኣርነት ግንባር ሊቀመንበር ካላ ቤታና ሆጤሳ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከሰይፌ ነበልባል ሬዲዮ ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ

Image
ከካላ ቤታና ሆጤሳ ጋር የተደረገውን ቃለ ምልልስ ከ5 ደቂቃ ጀምሮ  ይከታተሉ።

ጉዞ ኃይለ ማርያም - ከአረካ እስከ አራት ኪሎ

Image
በዮናስ አብይ የ43 ዓመቱ ጐልማሳ መንገሻ መንዳዶ የተወለደባትንና አድጐ የተማረባትን አነስተኛዋን የአረካ ከተማን ለቆ መኖርያውን በአርባ ምንጭ ከተማ ካደረገ ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ዛሬ የሥራ ጠባዩ በፈጠረለት አጋጣሚ ሙሉ ጊዜውንና ኑሮውን በአርባ ምንጭ ላይ በመመሥረቱ አልፎ አልፎ በአዕምሮው ውልብ ከሚሉበት ትዝታዎች በስተቀር ስለተወለደባት የአረካ ከተማ ሲያወሳ አይሰማም፡፡ ነገር ግን ስለተወለደባት ከተማ ከማይረሳቸው የልጅነት ትውስታዎቹ ውስጥ አንድ አስገራሚ ታሪክን ከተማሪነት ዘመኑ መዝዞ በፈገግታና ኩራት በተሞላበት ሁኔታ ሲያወጋ፣ ያድማጭን ጆሮ በጉጉት ሊያቆም እንደሚችል በቅድሚያ ከገጽታው ደማቅነት መረዳት ይቻላል፡፡ የታሪኩ ክስተት ወደኋላ 28 ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ 300 ኪሎ ሜትር በምትርቀው በአረካ ከተማና በነዋሪዎቿ ታላቅ የመደነቅ ስሜትን ስለፈጠረ  የአንድ ጎበዝ ተማሪን አስደናቂ ጉዳይ ያወሳል፡፡ መንገሻ በወቅቱ ከሚማርበት የአረካ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይልቅ ከከተማዋ ዕምብርት ሦስት ኪሎ ሜትር ርቀት ስለሚገኘው ዱቦ የካቶሊክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ስላለ አንድ ተማሪ ጉብዝና መስማትና ማውራት ይመስጠው ነበር፡፡ “በዚያ የሕፃንነት ዕድሜ ሁሉም ሰው ስለሱ ጉብዝና ብቻ ሲወራ ትዝ ይለኛል፡፡ እኔም በእኛ ትምህርት ቤት ውስጥ ካሉ ጐበዝ ተማሪዎች ይልቅ በዚያኛው ትምህርት ቤት ስላለው ጐበዝ ተማሪ ብሰማም ባወራም አልጠግም ነበር፤” በማለት የሚናገረው መንገሻ አገለለጹና ገጽታው ይህ ታሪክ እንኳን 28 ዓመታት ቀርቶ አሥር ዓመት የሞላው አይመስልም፡፡ በነዚያ ዘመናት ውስጥ እነ መንገሻ ከሚኖሩበት ከተማ አልፎ በድፍን ቦሎሶ ሶሬ በጉብዝናውና በቀለም ትምህርት አያያዙ “ያሳድግህ” ተብሎ

የሲዳማ የፖለቲካ ፓርቲዎች

ከታዛቢው ሲኣን በሲዳማ ጉዳዮች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ከመስጠት ያለፈ ስራ ስሰራ ኣይታይም የሲዳማ ዲያስፖራ የፖለቲካ ድርጅቶች የኢንተርኔት ላይ ኣንበሶች ናቸው ይሄ ቀጥዬ የማቀረበው ኣስተያየት የእኔ የግሌ ኣስተያየት ነው። ምናልባት በእኔ ማንነት ላይ ጥርጣሬ ቢኖር እኔ የመንግስት ደጋፊ ወይም ተቃዋሚም ኣይደለሁ፤ እንዲሁም የተቃዋሚዎች ደጋፊም ሆነ የተቃዋሚዎች ተቃዋሚም ኣይደለሁ። እኔ የሲዳም ህዝብ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መብቶች ስከበሩ ማየት የምሻ የሲዳማ ህዝብ ተቆርቋር ነኝ። እባካችሁ ከዚህ ባለፈ ሌላ ስም ኣትለጥፉብኝ ኣደራ። ስለ እራሴ ይህንን ያህል ካልኩ ወደ ጉዳዬ ልለፍ፦ በተለይ ካለፉት ሶስት ወራት ወዲህ ሲዳማ በፖለቲካ ትኩሳት ውስጥ ናት ማለት ይቻላል። በተለይ ከክልል ጥያቄ እና ከሃዋሳ ከተማ የወደፊት እጣ ፋንታ በምወሰኑ ጉዳዮች ላይ ህዝቡ ከመንግስት ጋር ተፋጦ መክረሙ ይታወሳል። ታዲያ ይህ ፍጥጫ ከፍጥጫነት ኣልፎ ወይም ኣፍትልኮ የወጣበትም ኣጋጣም ተከስቶ ነበረ በተለይ በወረዳዎች ኣከባቢ። የሆነ ሆኖ ዛሬ ግን ፍጥጫው እየረገበ ያለ ይመስላል። ይህንን ያነሳሁት ያለፈ ታሪክ ልተርክላችሁ ብዬ ኣይደለም፤ ያነሳሁበት ዋናው ምክንያት ስለ ሲዳማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የታዘብኩትን ጀባ ልላችሁ ብየ ነው። ምን ታዘብክ ብላችሁ ጠይቁኝ ታዲያ ! ኣዎን የሲዳማ የፖለቲካ ድርጅቶችን ብዙ እየታዘብኩ ነው። ለመሆኑ የሲዳማ የፖለቲካ ፓርቲዎች እነማናቸው ? ይመስለኛል ስለ ፓርቲዎቹ ማውራታችን ካልቀረ ስለ ማንነታቸው በስሱ ማንሳቱ የግድ ይመስለኛል። እኔ ከልጅነተ ጀምሮ የማውቀው ኣንዳንዴ ስለው ተቃዋሚ ስለው ደግሞ የመንግስት ደጋፊ እየሆነ ሁለት መልክ የሚይዘው የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ( ሲኣን ) ከቀድሞው ሲ

በሲዳማ ዞን የአማራጭ ኢነርጂ ልማት በመጠናከር ላይ ነው

Image
ሰሞኑን በሃዋሳ ከተማ በተካሄደው የደቡብ ክልል የውሃ ጉባኤ የቀረበው የ 2004 ኣ / ም የመምሪያው የስራ ኣፈጻጸም የተመለከተው ኣንድሪፖርት እንዳመለከተው በዞኑ ውስጥ በኣማራጭ ኢነርጂ ልማት ዘርፍ ኣበራታች ስራዎች ተከናውነዋል። መምሪያው በባጀት ኣመቱ ለማከናወን ካቀዳቸው 19 አዲስ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃ አምራቾች ማህበራት እንዲቋቋሙ በማድረግ ለ 3- ማህበራት ፕሬስና ሞልድ ተገዝቶ ድጋፍ ማድረጉ የተገለጸ ሲሆን፤ በ 19 ወረዳዎች በ 38 አማካይ ቦታዎች የማገዶ ቆጣቢ ምድጃ ላይ ለሕ ብረተ ሰቡ ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በመስጠት ከእቅዱ በላይ በመስራት 4500 የተሻሻሉ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎ አንዲሰራጩ በማድረግ በርካታ የዞኑን ነዋሪዎች ተጠቃሚ  ኣድርጓል ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በሁሉም ወረዳዎች 100 የሚሆኑ የቤተሰብ የሶላር ተጠቃሚ ማህበራት መደራጀታቸው ሲገለጽ፤ የኃይል አማራጭ ኢነርጂ አጠቃቀም ላይ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል። እንደሪፖርቱ ከሆነ የሶላር ኢነርጂ ተከላ እና የባዮ ጋዝ ግንባታ በተለያዩ ወረዳዎች የተካሄደ ሲሆን፤ ኣራት የአማራጭ ኢነርጂ ዳሰሳ ጥናት ም ተከናውነዋል።

ዘንድሮ ለሚካሄደው የአካባቢ ምርጫ ዝግጅት እየተደረገ ነው

Image
አዲስ አበባ ጥቅምት 9/2005 (ዋኢማ)  - ዘንድሮ የሚካሄደውን የአካባቢ ምርጫ ግልጽ፣ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ ዝግጅቶች እያደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የቦርዱ ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ይስማ ጅሩ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለጹት ምርጫውን ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ  ለማድረግ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች ከወዲሁ እየተከናወኑ ነው። በተለያየ ደረጃ የነበሩ የምርጫ ጣቢያዎችን በአዲስ መልክ በማደራጀት በኦሮሚያ፤ በትግራይ፤ በአማራና በደቡብ ክልሎች ለሚገኙ የምርጫ አስፈጻሚ አባላት  የአቅም ግንባታ ስልጠናመሰጠቱን  የገለጹት አቶ  ይስማ ለፖለቲካ ፓርቲዎችም በእጩዎች አቀራረብ ዙሪያ  ስልጠና ተሰጥቷል ብለዋል። የእጩ ተመራጮችና የመራጮች  ምዝገባ እንደዚሁም  ምርጫው የሚካሄድበት የጊዜ ሰሌዳ ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር በመወያየት  ወደፊት እንደሚወሰን አቶ ይሰማ ገልጸዋል። በአካባቢ ምርጫው የወረዳ፤ የቀበሌ ፤የማዘጋጃ ቤት፤ የከተማ አስተዳደርና የዞን ምክር ቤቶች አባላት እንደሚመረጡ የገለጹት አቶ ይስማ  ምርጫውን በስኬት ለማጠናቀቅ መላው ህብረተሰብ  የበኩሉን ተሳትፎ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።

በሀገሪቱ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በማዕድን ፍለጋና ልማት ላይ ተሰማርተዋል

Image
ሃዋሳ ጥቅምት 09/2005 ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቱ በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በማዕድን ፍለጋና ልማት ላይ መሰማራታቸውን የማዕድን ሚኒስትሯ ገለጹ፡፡ ስለማዕድን ኢንዱስትሪ ግልጽነት ኢኒሼቲቭ አሰራር ለበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ግንዛቤ ለማስጨበጥ በሀዋሳ ከተማ ትናንት በተዘጋጀው አውደ ጥናት ላይ ሚኒስትሯ ወይዘሮ ስንቅነሽ እጅጉ እንደገለጹት ባለሀብቶቹ በዑጋዴን፣ በመቀሌ፣ በአባይ፣ በኦሞና በጋምቤላ በርካታ ኩባንያዎች በማዕድን ቆፋሮ ላይ ተሰማርተዋል፡፡ ማዳበሪያ፣ መስተዋት፣ ሳሙናና ሌሎችን ለማምረት በግብዓትነት የሚጠቅሙ በርካታ የማዕድን ሃብቶች እንዳሉ ያስረዱት ሚኒስትሯ በነዳጅ ዘርፍም በተለያዩ ሥፍራዎች ፍለጋው መቀጠሉን ገልጸዋል፡፡  ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልካቸው የምርት ዓይነቶች የማዕድን ሃብት 20 በመቶውን እንደሚይዝና ለሀገሪቱ ዘላቂ ልማት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማጎልበት መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ብቻ የወርቅ ፣ የታንተለም፣ የጌጣጌጥና የመሳሰሉት የማዕድን ጥሬ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ ከ460 ሚልዮን በላይ ዶላር የውጭ ምንዛሬ መገኘቱንና በዚሀ ዓመትም ይህንን በእጥፍ ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ኢትዮጵያ በማዕድን ፍለጋና ምርመራ ስራ የረጅም ጊዜ ታሪክ ያላት ሀገር ናት ያሉት ሚኒስትሯ የማዕድን ሃብት አለኝታ ጥናት በተለያዩ ወቅቶች በውጭና በሀገር ውስጥ የስነ ምድር ባለሙያዎች ሲከናወን መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ እስከአሁን በተደረጉ ጥናቶች የኢንዱስትሪ፣ የኮንስትራክሽን፣ የጌጣ ጌጥ ፣ የወርቅ፣ የብረታ ብረት፣ የሃይድሮ ካርቦን ክምችትና የጂኦተርማል ማዕድናት መኖራቸው መረጋገጡን ጠቁመዋል፡፡  የማዕድን ኢንዱስትሪ

የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በሚደረገው ጥረት ሁሉም የድርሻውን መወጣት ይጠበቅበታል

ሃዋሳ ጥቅምት 09/2005 የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅና ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የድርሻቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ገለፀ፡፡ በሀዋሳ ሲካሄድ የቆየው የክልሉ ትምህርት ቢሮ የ2004 አጠቃላይ የትምህርት ጉባዔ ትናንት ማምሻውን ተጠናቋል፡፡ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች፣ ባለድርሻ አካላትና የትምህርት አመራሮች ማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡ የቢሮው ኃላፊ አቶ መሃመድ አህመዲን በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ጥራት ለማስጠበቅ ሁሉም የህብረተሰብ ከፍልና ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል፡፡ ክልሉ ከፍተኛ በጀት በመመደብ የሳይንስ ዘርፍ ትምህርትን ለማጠናከር ኮምፒዩተሮች እንደሟሉና የቤተ ሙከራ ግብአቶችን በማቅረብ አበረታች ስራ እያከናወነ ነው ብለዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመስራት ለትምህርቱ ጥራት ልዩ ትኩረት በመስጠትና በአግባቡ እንዲመራ በማድረግ በኩል ለሌሎች አርአያ እንዲሆን የሚያስችል ስራ ማከናወኑን አመልከተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በክልሉ ከ30 ሺህ በላይ የወላጅና የመምህራን ህብረት አመራሮች በትምህርት ቤቶች በመደራጀት በየጊዜው የተለያየ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጣቸው መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ የተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል ለትምህርት ቤቶች ድጋፍና ክትትል በማድረግ የትምህርት ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ በማድረግ በኩል አበረታች ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል፡፡ በትምህርታቸው የተሻለ ውጤት ካመጡት ተማሪዎች መካከል ተማሪ ቤተልሄም ታሪኩ፣ ገዛህኝ አበራ፣ ኢዩኤል ተከተልና ተማሪ ዲቦራ አበራ በሰጡት አስተያየት በትምህርት ቤቶች የተፈጠሩ አደረጃጀቶች፣ የመምህራን የዕለት ተዕለት ክትትልና አስፈላጊ የትምህርት ግ

ሲዳማን ጨምሮ በደቡብ ክልል በተያዘው ዓመት ከ116 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ይለማል

Image
አዋሳ ጥቅምት 08/2005 በደብብ ክልል በተያዘው የምርት ዘመን ከ116 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። ለተከላው ከ320 ሚሊዮን በላይ ችግኝ ይዘጋጃል።  በክልሉ ግብርና ቢሮ የመንግስት ኮሚኒኬሽን የስራ ሂደት ኦፊሰር አቶ አያሌው ዘነበ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በክልሉ ቡና አብቃይ በሆኑ ወራዳዎች 116 ሺህ 648 ሄክታር መሬት በስግሰጋና በአዲስ በቡና ይለማል። በእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በክልሉ ቡናን በብዛትና በጥራት በማምረት የሚገኘውን የውጪ ምንዛሪ መጠን ለማሳደግ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።  በምርት ዘመኑ በክልሉ በቡና የተሸፈነውን መሬት መጠን 22 በመቶ ለማሳደግ በተያዘው ግብ መሰረት ምርጥ የቡና ዘር በማሰባሰብ በግብርና ምርምር ማዕከላት፣ በመንግስት፣ በባለሀብትና በአርሶ አደሩ የችግኝ ጣቢያ ከ122 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ ምርጥ የቡና ዘር በማፍሰስ የችግኝ ዝግጅት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።  በቡና ተከላ ስራ ለሚሰማሩ ከ438 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች በቡና ማሳ ዝግጅት ተከላ እንክብካቤ አሰባሰብና አከመቻቸት ዙሪያ በተግባር የታገዘ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑንም አቶ አያሌው ገልጸዋል።  በክልሉ በቡና ከለማውና ለምርት ከደረሰው 349 ሺህ948 ሄክታር ማሳ ከ3 ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱንና የቡና ምርታማነትን በሄክታር 10 ነጥብ 5 ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።  ዘንድሮ በቡና ለሚሸፈነው ከ116 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት 320 ሚሊዮን 895 ሺህ 915 የቡና ችግኝ ዝግጅት በመደረግ ላይ እንደሚገኝ አቶ አያሌው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ገልጸዋል።

ልዩነት ለዘለዓለም ይኑር!

ሰላም! ሰላም! እንዴት ናችሁልኝ? ‹‹እንደርሳለን ብለን ከመሸ ተነስተን፣ ስንገሰግስ ነጋ ምንድን ነው የሚሻለን?›› አለችላችሁ አንዷ አዝማሪ። እውነቷን ነው እኮ! ‹‹በዚህ አካሄዳችን እንኳን ልንደርስ የት እንደምንሄድም የምናውቅ አንመስልም፤›› ከእንቅልፌ እንደተነሳሁ ማንጠግቦሽን እንዲህ ብላት፣ ‹‹ኧረ ተረጋጋ። እንዴ ቅዠትና እውነትን ለይ እንጂ፤›› አለችኝ። ስንት መልካም ጅማሮዎች ባሉት በዚህ ጊዜ የእኔስ እንዲህ ማለት አይገርማችሁም? ‹‹የእኔ ባትሆኝ ይቆጨኝ ነበር፤›› አልኩ። የእውነት የእኛ አልሆን እያለን የሚያስቆጨን በዝቷል። ሌላ ምንም ሳይሆን የገዛ ኑሯችንን መውሰድ ትችላላችሁ። እኛ እየኖርነው የእኛ ይመስላል? እሱ በፈለገው እንጂ እኛ በፈቀድነው እንመራዋለን? ኧረ ጣጣ ነው ዘንድሮ ወገኖቼ! እውነቴን ነው የምላችሁ ልቤ ክፉኛ የሚዝለው እንዲህ እንዲህ ሳስብ ነው። የደላላ ልብ ጥቁር ድንጋይ ነው ያለው ማን ነው? ‹‹እኛም እኮ አንዳንዴ ሰው ነን፤›› አለች አሉ ጦጣ። ‘እኛም በቤታችን እህህ አለብን’ ሲባል ባትሰሙ ነው? ይህችን እንኳን የእኛ ሠፈር አባባል ስለሆነች ላትሰሙዋት ትችላላችሁ። አንድ ደፋር ነው አሉ፣ ‹‹ማንም ያለሙያውና ዕውቀቱ ስንት ቦታ እየገባ ነገር ሲያበላሽ እየታለፈ የእኛ ሠፈር በዚህ አባባል አትጠቆርም፤›› ብሎ የለፈፈው። ወይ የዘመኑ ፈጠራ! ሁሉንም ነገር ካዛመድነው እዚህ አገር ስለሙያና ባለሙያው ብዙ ይወራል። በየዘርፉ ለሥራቸው ባላቸው ትጋት ምሥጋና የምንቸራቸው ሰዎች ጥቂት አይደሉም እኮ። ባናስተውለው ነው እንጂ! ታዲያ በዚያው ልክ ያለ ቦታው ገብቶ የሚያደናቁረውን ስታዩ የማማረሪያ ቃላት አይበቋችሁም። በነገራችን ላይ የዘንድሮ ቃሪያ አንሰፍስፎ አላቃጥል ያለን ለምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? ያለቦታቸው የገቡ የሰው ቃሪያዎች በ

Another busy day in Warancha and the surrounding area of Awassa.

Image
Best Day Yet! Another busy day in Warancha and the surrounding area of Awassa. The children greeted us with a song and game as we walked onto the field. They were so excited to see us again. We taught them songs and in return, they sang for us. We played “Minute to Win It,” passed life savers on spaghetti noodles, and balanced 5 die on popsicle sticks. Our team performed two skits: birth of Christ with shepherds and then birth of Christ with wise men. Then the children re-enacted both skits. They are stars in the making and really played their parts well…even down to the expressions on their faces when the host of angels came to proclaim Christ’s birth. We ended our morning with another soccer game while the little ones played other games. We left Warancha at noon, ate lunch and then visited Shalom Orphanage just down the street. This is the orphanage from where Doug (our team leader from Riverside) adopted his son Zebene, 7 months ago. Arrangements had been made prior to

Infographic: The Power of Cooperatives Explained

Image
Anja Tranovich Editor and Media Relations Specialist, ACDI/VOCA Infographic: The Power of Cooperatives Explained Posted: 10/16/2012 10:27 am This World Food Day, October 16, celebrates the power of cooperatives, "Key to Feeding the World." Why co-ops? By banding together in a co-op, farmers can buy inputs, like fertilizer and seed, directly from providers, saving expensive middleman costs. They can efficiently learn new techniques. They can share costs of storage or processing and bulk their crop to sell to larger companies who want products measured in tons not in bushels. Whether in grain or coffee, cooperatives connect farmers to markets and to each other. Take the case of the Ferro coffee cooperative in Ethiopia. The Ferro co-op accomplished a remarkable feat when it connected its rural, smallholder farmers to the global market for specialty coffee, and the co-op's dry-processed coffee was designated a Starbucks' Black Apron

Gerontocracy as a tradition and a mirror for the future (The case of Sidama)

by John  HAMER Anthropology holds up a great mirror to man and lets him look at himself in his infinite variety. [Kluckholm 1949:11] Years ago Clyde Kluckholm published a book titled 'Mirror for Man". In it he explained how studies of nonwestern societies '... show the great variety of solutions ...' that have been developed, as well as '...the variety of meanings ...' that have been conceived to resolve human problems (ibid:15). This world panorama of differing life styles became a way of learning '... what works and what doesn't ...' Since then, and specially now with the popularization of 'cultural diversity,' the discovery has focused, for the average person, on such peripheral aspects of difference as tasting foods and musical forms. Seldom, however, have westerners been willing to look seriously at the possibility of experimenting with different forms of authority, social, and economic practices observed in the cultures of other