Posts

የኢጋድ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ምላሽ መካኒዝም ድንበር ተሻጋሪ የሰላም ጉባዔ በሐዋሳ ይካሄዳል

Image
ሐዋሳ ታህሳስ 4/2011 የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት/ኢጋድ/ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ምላሽ መካኒዝም ድንበር ተሻጋሪ የሰላም ጉባዔውን ከነገ ጀምሮ በሐዋሳ ያካሂዳል፡፡ የኢጋድ ቅድመ ማስጠንቀቂያና ምላሽ መካኒዝም የሕዝብ ግንኙነት ኦፊሰር ወይዘሮ ትዕግሥት ኃይሉ ለኢዜአ እንደገለጹት በኢትዮጵያና በኬንያ ሰላምና ልማት ዙሪያ የሚያተኩረው ጉባዔ በከፍተኛ ኃላፊዎች ደረጃ ለሁለት ቀናት ይደረጋል፡፡ በቅርቡ በሞያሌና በጂንካ በኢትዮጵያና በኬንያ ማህበረሰቦች ደረጃ በተደረገው ውይይት የተነሱ ዓበይት ጉዳዮች የጉባዔው ዋነኛ አጀንዳ እንደሚሆኑና ውሳኔ እንደሚሰጥባቸው ይጠበቃል ብለዋል፡፡ በሰላም ሚኒስትር ይመራል ተብሎ በሚጠበቀው በዚህ ጉባዔ ላይ የኬንያ አቻቸውና የኢጋድ ሥራ አስፈጻሚ እንዲሁም የአገሮቹ ተወካዮች እንደሚሳተፉበት ተናግረዋል፡፡ ከኢትዮጵያ የኦሮሚያ፣ የደቡብና የሶማሌ ክልሎች ርዕሳነ መስተዳድርና ከኬንያ የቱርካናና የመርሳቤት አስተዳደሮች ከፍተኛ አመራሮች ይገኙበታል ተብሎ እንደሚጠበቅም ወይዘሮ ትዕግሥት ገልጸዋል፡፡ ምንጭ 

በሰብዓዊ መብት አያያዝ ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አሕመድ ያስተላለፉት መልዕክት

Image
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው ሀገራችን ኢትዮጵያ በለውጥ ጉዞ ላይ መሆኗን ገልጸዋል። በዚህ የለውጥ ጉዞዋም የሚለወጡ ነገሮች አሏት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ከዚህ ውስጥም የዜጎች የሰብዓዊ መብት አያያዝ አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያውያን በየዘመናቱ ታግለው የመንግሥት ለውጥ እንዲመጣ ካደረጉባቸው ምክንያቶች አንዱ ሰብዓዊ መብታቸውን የሚያከብር ሥርዓት ለማስፈን እንደነበር አስታውሰው፥ የሰብዓዊ መብት አያያዝም ሆነ ሌሎች ዴሞክራሲያዊ መብቶች በመሠረታዊነት እውን የሚሆኑት ከግለሰቦች ፍላጎት ይልቅ የጋራ ፍላጎት በወለዳቸው ተቋማት መመራት ሲጀምር መሆኑንም ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው ተዓማኒ የሆኑ የዴሞክራሲያዊና የፍትሕ ተቋማት ባልተመሠረቱበት ሁኔታ፥ ግለሰቦች እንዳሻቸው ሲሆኑ መመልከት በታሪኩ በተደጋጋሚ ለተመለከተው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንግዳ እንደማይሆንም አንስተዋል። ሕዝቡ ሁልጊዜም አምባገነናዊ ሥርዓትን ለመገርሰስ ሲታገልና መሥዕዋት ሲሆን ግፍ እንዲቆም፣ ፍትሕ እንዲሰፍን እንጅ፥ ሌሎች ግፈኞችን ለመተካት አይደለምም ነው ያሉት። በሕዝብ ትግል ሥልጣን ላይ የወጡ አካላት ግን ከራሳቸው ፍላጎት ውጭ የሕዝብን ፍላጎት ማሟላት አለመቻላቸውን ጠቅሰው፥ ሕዝቡ ከነገ ዛሬ ይሻሻላል ብሎ ቢጠብቅና ድምፁን ቢያሰማም ችግሩ እየባሰ መሄዱንም አውስተዋል። በተለይም የዴሞክራሲ ምኅዳሩ እየጠበበ፣ ዜጎች በብሔራቸውና በያዙት የፖለቲካ አስተሳሰብ ምክንያት የሚደርስባቸው በደል እየከፋ፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቱ እየባሰና ሙስና ይበልጥ እየሰፋ መምጣቱንም ጠቅሰዋል። እነዚህና መሰል ሁኔታዎችም ህዝቡን በደልና ግፍ በቃን ብሎ እንዲነሳ አድርገውታልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ። በሃገር ላይ ከፍ ያለ ወንጀል የፈጸሙ ቡድኖች በነጻነት ሲንቀሳቀሱ

ቡና ላኪዎች በረቀቀ መንገድ አዲስ የቡና ስርቆት ወንጀል እየተፈጸመ መሆኑን አስታወቁ

Image
ወደ  ኮሪያና አውስትራሊያ በተላከ ቡና ላይ የስርቆት ወንጀል በመፈጸሙ ክስ ሊመሠረት ነው ቡና ላኪዎች በረቀቀ መንገድ በኮንቴይነር ታሽጎ ከተላከ ቡና ላይ ስርቆት እየተፈጸመባቸው መቸገራቸውን፣ ኢትዮጵያም በዚህ ችግር ሳቢያ በገዥዎች ዘንድ አመኔታን የሚያሳጣ አሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ መውደቋን ገለጹ፡፡ ከዚህ ቀደም ‹ቅሸባ› በሚባል ስያሜ የሚታወቀው ወንጀል በተሽከርካሪዎች  የሚጓጓዘውን ቡና ሸራ በመቅደድ ይፈጸም የነበረው አድራጎት፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መልኩን ቀይሮ ወደ ኮንቴይነር ‹ቅሸባ› መሸጋገሩን ላኪዎች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ለሪፖርተር ስለጉዳዩ ያብራሩት አቶ ፈይሰል አብዶሽ ዮኒስ የቴስቲ ኮፊ ትሬዲንግ ኩባንያ መሥራችና ዳይሬክተር ሲሆኑ፣ ቡናቸውን ከላኩባቸው አገሮች በተለይም ወደ ኮሪያ ከተላከው ቡና 25 ቁምጣ ወይም 15 ኩንታል ቡና ከአንድ ኮንቴይነር መጉደሉን ቡናውን የገዛው ኩባንያ እንዳሳወቃቸው ተናግረዋል፡፡ ወደ አውስትራሊያ ሲድኒ የተላከውም ቡና እንዲሁ ጉድለት እንደታየበትና ምን ያህል ጉድለት እንደተከሰተ ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝ አቶ ፈይሰል ገልጸዋል፡፡ እንዲህ ያለው ጉዳይ በኮንቴይነር በተላከ ቡና ላይ ሲገጥማቸው የመጀመርያቸው መሆኑንም አቶ ፈይሰል ሳይጠቅሱ አላለፉም፡፡ ‹‹እኔ ኮሪያና አውስትራሊያ ሲድኒ ነው የጫንኩት፡፡ ከኮሪያው 25 ቁምጣ ወይም 15 ኩንታል ቡና መጉደሉን አስታውቆናል፡፡ የሲድኒውም ጉድለት እንዳለ ኢሜይል ተደርጎልናል፡፡ ትልቅ ችግር ውስጥ ነን፡፡ ሥርዓት አልበኝነቱ ቅጥ አጥቷል፤›› ያሉት አቶ ፈይሰል፣ ይህ ጉዳይ አሳሳቢ እየሆነ የመጣ አዲስ ክስተት እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ ይህ በመሆኑም ቡናውን ወደ ጂቡቲ እንዲያጓጉዙ በተዋዋሉት አካል ላይ፣ ቡናው ወደ ጂቡቲ ከመላኩ በፊት የቡናና ሻይ ባለሥልጣን ተወካ

በፕሪሚየር ሊጉ ድሬዳዋ እና ሃዋሳ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል

Image
  ኤፍ ቢ ሲ ) 5ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በተለያዩ ከተሞች ተካሂዷል። ( ድሬዳዋ ላይ ድሬዳዋ ከተማ ደደቢትን አስተናግዶ 2 ለ 0 አሸንፏል። ጅማ አባ ጅፋርን ያስተናገደው ስሑል ሽረ ደግሞ ጨዋታውን ያለምንም ጎል በአቻ ውጤት አጠናቋል። ሃዋሳ ላይ ደግሞ ሃዋሳ ከተማ አዳማ ከተማን አስተናግዶ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ ጨዋታ ደግሞ ኢትዮጵያ ቡና ከወላይታ ዲቻ ተገናኝተዋል። ጨዋታው በአቻ ውጤት ሲጠናቀቅ፥ ካሉሻ አልሃሰን ለኢትዮጵያ ቡና በረከት ወልዴ ደግሞ ለወላይታ ዲቻ ጎሎቹን አስቆጥረዋል።

Sidama Buna 2-1 Kidus Giorgis #EPL 2018/19

Image

ለዶክተር ወላሳ ላዊሶ በሀዋሳ ሚሊኒየም አደባባይ ታላቅ አቀባበል ይደረግላቸዋል ተባለ

Image
ፎቶ ከየሲዳማ ዞን ባ.ቱ.መ.ኮሙ የሲዳማ ዞን ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊዎች በጋራ በሰጡት መግለጫ፤  ለዶክተር ወላሳ ላዊሶ በሀዋሳ ሚሊኒየም አደባባይ ታላቅ አቀባበል ይደረግላቸዋል ብለዋል  ፡፡ ዝርዝር መግለጫውን ከታች ያንቡ፤   የተወደዳችሁ የሲዳማ ብሔር ተወላጆች፣ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም በሀገራችን በተለያዩ ክልሎች የምትገኙ የሲዳማ ብሔር ወዳጆች በሙሉ በቅድሚያ የሲዳማ ብሔር የልማት አርበኛና ታዋቂ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ወላሳ ላዊሶ እና በእርሳቸው የሚመራ ከስደት ተመላሽ ቡድን እንዲሁም የሲዳማ ሚዲያ ኔትወርክ (SMN) የቦርድ አባላት ወደ እናት ሀገራቸው ኢትዮጵያ ለመመለስ በመብቃታቸው እንኳን ደስ አላችሁ በማለት የተሰማንን ታላቅ ደስታ አንገልፃለን፡፡  ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሀገራችን ኢትዮጵያ ፖለቲ ካ በያዙት አቋምና በሌሎች ምክንያቶች ከእናት ሀገራቸው ተገፍተው ለዘመናት በስደት ይኖሩ የነበሩ በርካታ ኢትዮጵያውን ወደ እናት ሀገራቸው ተመልሰው በሰላማዊ መንገድ የመንቀሳቀስ እድል አግኝተዋል፡፡ ይህንንም እድል ተጠቅመው ወደ እናት ሀገራቸው በርካታ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ የተለያዩ ሚዲያዎች እንዲሁም የልማት አርበኞች በመመለስ ላይ ይገኛሉ፡፡  ከእነዚህ መካከል አንዱ የሆኑት እውቁ የምጣኔ ሀብት ባለሙያው እና ከራሳቸው ጥቅም በላይ የህዝብን ጥቅም የሚያስቀድሙት የሲዳማ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጅ ዶክተር ወላሳ ላዊሶ የፊታችን እሁድ በቀን 30/3/2011 ወደሚናፍቋት ወደ ትውልድ ዞናቸው ሀዋሳ ከተማ ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በዶክተር ወላሳ

ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአምስት ሰዎች ህይወት አለፈ

Image
አዲስ አበባ፣ ህዳር 29፣ 2011( ኤፍ.ቢ.ሲ) ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአምስት ሰዎች ህይወት ማለፉን የምዕራብ አርሲ ዞን የትራፊክ መምርያ አስታወቀ ። ዛሬ ጠዋት 1 ሰዓት ከ30 ላይ በውጭ ሀገር ሆነው  ለሲዳማ ህዝብ እኩልነት ሲታገሉ የቆዩትን እነ ፕሮፌሰር ወላሳ ላዊሶነንና ሌሎች   የመብት ተሟጓቾችን  ለመቀበል ሲጓዙ የነበሩ ሰዎችን የያዘ ላንድ ኩሩዘር  ከአርሲ ነጌሌ ወደ ሻሻመኔ በመጓዝ ላይ ከነበረ አይሱዙ የጭነት መኪና  ጋር  አርሲ ነጌለ ወረዳ ቀርሳ እላላ ቀበሌ በመጋጨታቸው የደረሳ አደጋ መሆኑን የምዕራብ አርሲ ዞን የትራፊክ ዲቪዥን ሀላፊ ኢንስፔክተር ጎሴ ድኮ ገልፀዋል፡፡ በዚህ አደጋም የአምስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በአንድ ሰዉ ከባድ የአካል አደጋ ደርሷል፡፡ የተጋጩት ሁለቱ መኪናዎች  ሙሉ በሙሉ እንደወደሙ የገለፁት ኢንስፔክተሩ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ ነዉ ብሏል፡፡ ምንጭ