Posts

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በአየር ንብረት ለውጥና በምግብ ዋስትና ላይ ያተኮረ የምርምርና የትምህርት መርሀ ግብር መጀመሩን አስታወቀ

Image
 የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከጀርመኑ ሆኸንየም ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአየር ንብረት ለውጥና በምግብ ዋስትና ላይ ያተኮረ የምርምርና የድህረ ምረቃ ትምህርት መርሃ ግብር መጀመሩን አስታወቀ፡፡ የአየር ንብረት ለውጥ በምግብ ዋስትና ላይ በሚያሳድረው ተጽዕኖና መፍትሄዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው፡፡ የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ተስፋዬ አበበ እንደገለጹት፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለው ጥረት በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ተግዳሮት እየገጠመው ነው። "ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ሰፊ ጥናትና ምርምር ማድረግና በዘርፉ የተማረ የሰው ኃይል ማፍራት ያስፈልጋል" ብለዋል። ለእዚህም የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከጀርመኑ ሆኸንየም ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የአየር ንብረት ለውጥ በምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ላይ እያሳደረ ያለውን ተፅዕኖ ለመፍታት የሚያስችል ፕሮጀክት ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ገለጻ በፕሮጀክቱ 14 የምርምር ሥራዎች የሚካሄዱ ሲሆን በዩኒቨርሲቲዎቹ 12 ባለሙያዎች የዶክትሬት ዲግሪ ትምህርት እየተከታተሉ ይገኛሉ። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶክተር ስንታየሁ ይግረም በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ በ2030 ከተያዙ 17 ዘላቂ የልማት አጀንዳዎች መካከል ሰባቱን ለማሳካት የተቀረጸ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በምግብ ዋስትና፣ በአየር ንብረት ለውጥና በትምህርት ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን የገለፁት አስተባባሪው በጀርመን መንግስት በተመደበ በጀት ተግባራዊ እንደሚደረግ ተናግረዋል። በጀርመን ሆኸንየም ዩኒቨርሲቲ በአየር ሁኔታ ትንበያ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን እየሰሩ ያሉት

በሲዳማ ዞን በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች መያዛቸው ተገለጸ

Image
በደቡብ ክልል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደቡብ ክልል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ። በቁጥጥር ስር የዋሉትም 10 የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች፣ ሁለት ቦምቦች እና 600 ጥይቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም 3 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ቡና በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። ፎቶ ከ ደህረ ገጽ የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መረጃ ኢንተለጀንስ ዳይሬክተር ኮማንደር ጉራማይሌ ጉራኦ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ የክልሉ ፖሊስ ባደረገው ክትትል ነው መሳሪያዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት። የጦር መሳሪያዎቹ በህገ ወጥ መንገድ ከደቡብ ሱዳን ጠረፍ የገቡና በሲዳማ ዞን ሲዘዋወሩ በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ኮማንደር ጉራማይሌ ገልፀዋል። በተጨማሪም በቤንች ማጂ ዞን በከፋ እና በሸካ ዞኖች በ10 አይሱዙ ተሽከርካሪዎች ተጭኖ፥ በህገ ወጥ መንገድ በመዘዋወር ላይ የነበረ 3 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚገመት ቡና  በቁጥጥር ስር ውሎ ለመንግስት ገቢ መደረጉን አስታውቀዋል። ቡናውን ጭነው የነበሩ 12 አሽከርካሪዎች እና ረዳቶች ጉዳያቸው በህግ እየተጣራ እንደሚገኝም ኮማንደር ጉራማይሌ አስታውቀዋል። እንደ ኮማንደር ጉራማይሌ ገለጻ፥ በሩብ ዓመቱ በክልሉ ከ4 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ ቶርሽን ጫማዎች፣ የሞተር ሳይክል እና የመኪና ሞተር መለዋወጫዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች እንዲሁም አዲስና ልባሽ ጨርቆች መያዛቸውን ተናግረዋል። የኮንትሮባንድ እቃውን ጭነው በህገ ወጥ መንገድ ሲያጓጉዙ የነበሩ አሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ነው ኮማንደር ጉራማይሌ የገለፁት።

በሰራ ለሚያምነው የሲዳማ ህዝብ ከዚህም በላይ ይባልለታል!

Image
በሰራ ለሚያምነው የሲዳማ ህዝብ ከዚህም በላይ ይባልለታል! የኣበራ ቶሸ የሲዳማን ህዝብ የሰራ ባህል በማሞገስ የተቀኘላቸው ዜማ

ሰሞኑን ከኦሮሚያ ክልል ባሌ ጎባ ዞን የተፈናቀሉት ቁጥራቸው ከኣምስት ሺህ በላይ የሚሆኑ የሲዳማ ተወላጆች በምግብ እና በመጠለያ እጦት ተቸግረዋል

Image
  ሰሞኑን ከኦሮሚያ ክልል ባሌ ጎባ ዞን የተፈናቀሉት ቁጥራቸው ከኣምስት ሺህ በላይ የሚሆኑ የሲዳማ ተወላጆች በምግብ እና በመጠለያ እጦት ተቸግረዋል። ፎቶ ለዝርዝር ወሬውን እዚህ ይጫኑ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት አያያዝ እንዲስተካከል እንግሊዝ ጥያቄ አቀረበች

Image
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ እየተከሰተ ካለው ቀውስ ጋር ተያይዞ እየተፈጠሩ ያሉ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ችግሮች እንዲስተካከሉ እንግሊዝ ጠየቀች፡፡   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሒሩት ዘመነ ከእንግሊዝ አምባሳደር ሱዛና ሞርሄድና ከኤምባሲው የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ባለፉት ሁለት ዓመታት በአገሪቱ እየተከሰተ ካለው ቀውስ ጋር ተያይዞ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ችግር እንዳለ፣ ኢትዮጵያም ይህን ችግር እንድታስተካክል እንግሊዝ ምክረ ሐሳብ ማቅረቧ ታውቋል፡፡ ይህ ምክረ ሐሳብ የቀረበው ኢትዮጵያና እንግሊዝ ለአራተኛ ጊዜ በሰብዓዊ መብቶች ላይ ያተኮረ የጋራ ውይይት፣ ሰኞ ኅዳር 4 ቀን 2010 ዓ.ም. በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡ በውይይቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሒሩት ዘመነ፣ በኢትዮጵያ የስደተኛና ከስደት ተመላሽ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ተወካዮች፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተወካዮች፣ በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር ሱዛና ሞርሄድና የኤምባሲው የሥራ ኃላፊዎች፣ የብሪታኒያ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዲኤፍአይዲ) ዳይሬክተሮችና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ተገኝተው ነበር፡፡ የውይይቱ አጀንዳዎችም የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ፣ ስደት፣ የመንግሥት ተጠያቂነትና ግልጽነት ነበሩ፡፡ የሁለቱ አገሮች የጋራ ውይይት የተካሄደው በዝግ ቢሆንም፣ የሪፖርተር ምንጮች እንደጠቆሙት በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ያሉ ችግሮችን የእንግሊዝ መንግሥት ተወካዮች በዝርዝር አውስተዋል፡፡ አንድ የእንግሊዝ ዲፕሎማት ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ስደተኞችን በማስተናገድ ግንባር ቀደም አገር ብትሆንም በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ችግሮች አሉባት፡፡ ‹‹ይህንን ያህል የስደተኛ