Posts

የኡጋንዳው ኤንኣር ኣኤም/NRM/ ፓርቲ በፖለቲካ ስልጣን ላይ ለረዥም ኣመታት እንዴት መቆየት እንደምቻል ከኢሕኣዴግ ልምድ ልቀስም መሆኑ ተሰማ

Image
የኡጋንዳው ኤንኣር ኣኤም/NRM/ ፓርቲ  ኢሕኣዴግ ላለፉት ሁለት ኣስርተ ኣመታት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ስልጣን ላይ ልቆይ የቻለበትን ምስጥር እንዲያካፍለው የፓርቲውን ኣባላት መጋበዙን ኦብዘርቨር የተባለው የኣገሪቱ ጋዜጣው ዛሬ ባወጣው እትሙ ላይ ኣስነብቧል።  “We are inviting someone from the ruling party of Ethiopia to take us through discipline and party cohesion and then explain to us how their party has managed to be in power for all this time,” Lumumba said. ዝርዝር ዜናውን ከታች ያንቡ፦    NRM consults Ethiopia on holding onto power All government departments, ministries and local government authorities will be held to account before the NRM retreat at Kyankwanzi, the party’s secretary general has said. In an interview at Parliament on Wednesday, Justine Kasule Lumumba said that during the February 7-15 retreat, the MPs would also hear from political experts from abroad about how to grow Uganda’s economy and strengthen the NRM’s hold on power. Among other things, the party wants to use the retreat to know how much the NRM government has delivered on President Museveni’

Election 2015 Update: Ethiopia's top oppostion banned by Govt -

Image
Election 2015 Update: Ethiopia's top oppostion banned by Govt -

የገዥው ፓርቲ ከተሞችን የማስፋፋት እቅድ ይፋ ተደረገ

Image
ሃዋሳ ከተማ እኣኣ 2003 ሃዋሳ ከተማ እኣኣ 2014 የኢትዮጵያ ከተሞችን አቅምና ቁጥርን ለማሳደግ የሚያስችል እቅድ ይፋ ተደረገ አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2007 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ከተሞች አቅምና ቁጥርን ለማሳደግ የሚያስችል እቅድ ይፋ ተደረገ ። እቅዱ በከተማ ልማትና ቤቶች ኮንስትራክሽንና በአለም ባንክ የስታስቲክስ ኤጀንሲ በጋራ የተሰራ ነው። በሁለተኛው የእድገትና ትርንስፎርሜሽን እቅድ ዘመን ከተሞችን ለኗሪዎች ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እንደሚሰሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ  በመድረ ኩ   ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉትም ጥናቱ የሌሎች ሀገራት ምርጥ ተሞክሮዎችን ሀገሪቱ እንድታይ ለማድረግ መሞከሩ የሚመሰገን ነው። አክለውም በተለይ በዚህ ወቅት ሀገሪቱ 2ኛውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ እያዘጋጀት ባለችበት ወቅት መሆኑ ደግሞ ያላየቻቸው ነገሮች ካሉ እንድታይ ያግዛታል ያሉት። ኢትዮዽያን እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2025 መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ የሚደረገው ጥረት  ከተሞችን በማሳደግና ቁጥራቸውን በማብዛት መደገፍ እንዳለበት ዛሬ የአለም ባንክ ይፋ ያደረገው ጥናት ይናገራል። የበርካታ የሀገራችን ከተሞች ፈተና የሆነው የመሰረተ ልማት ችግር፤ የሃይልና የመብራት እጥረት፤ ዘመናዊ የደረቅና የፈሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ ስርአት መስተካከል እንዳለበት የመኖሪያ ቤትና የስራ እድል ፈጠራው ላይም ሊታሰብበት እንደሚገባ ይጠቁማል። ከዚህ አንጻር የከተሞቹ እድገት ከመምጣቱ በፊትና ከተሞቹን ዝግጁ ከማድረግ አንጻር ምን መሰራት እንዳለበት ጥናቱ የሚጠቁም መሆኑን ነው በአለም ባንክ ከፍተኛ የከተማ ልማት ኤክስፐርት አቶ አበባው አለማየሁ የተናገሩት። ጥናቱ ሀ

Sidaamu_Fidalla1

Image

ቦርዱ በአቶ ትዕግስቱ ለሚመራው የአንድነት ፓርቲ እና በአቶ አበባው ለሚመራው መኢአድ ፓርቲ ዕውቅና ሰጠ

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2007 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጽህፈት ቤት በአመራር ውዝግብ ውስጥ በነበሩት አንድነት ለፍትህ እና ለዴሞክራሲ ፓርቲና በመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ዙሪያ ውሳኔ አሳለፈ። አንድነትን በተመለከተ አቶ ትዕግስቱ አወሎ የፓርቲው ህጋዊ ሊቀመንበር ናቸው ብሏል። በመኢአድ በኩል ለአቶ አበባው መሃሪ የፓርቲው የህጋዊ ፕሬዚዳንትነት ዕውቅናም ሰጥቷል። አንድነትም ሆነ መኢአድ ቦርዱ ዕውቅና በሰጣቸው መሪዎች እየተመሩ በምርጫው መሳተፍ እንደሚችሉም ነው የተወሰነው። መግለጫውን የሰጡት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ፀሃፊ አቶ ነጋ ዱፌሳ ቦርዱ ለሁለት የተከፈሉትን የሁለቱንም ፓርቲዎች አመራር ችግራቸውን ለመፍታት የተሰጣቸውን ጊዜ ለመጠቀም ያከናወኗቸውን ተግባራት በጥልቀት መመርመሩንም ተናግረዋል። ቀደም ሲል የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አንድነትና መኢአድ በውስጣቸው የተከሰተውን ችግር ፈትተው እንዲመጡ የ14 ቀናት ጊዜ ሰጥቶ የነበር ሲሆን፥ ቦርዱ የጊዜውን መጠናቀቅ ተከትሎ በቀጣዮቹ ሁለት ቀናት የመጨረሻ ውሳኔ ለማሳለፍ በዛሬው ዕለት ቀጠሮ መያዙ ይታወሳል። በአቶ በላይ ፈቃዱ የሚመራው አንድነት የምወያየውም ሆነ የማካሂደው ጠቅላላ ጉባኤ የለም በማለት ባለፈው አርብ በሰጠው መግለጫ ሲያስታወቅ፣ በአቶ ትዕግስቱ አወሉ የሚመራው የአንድነት ቡድን ደግሞ ቅዳሜ እለት ባካሄደው ጉባኤ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንቱን ጨምሮ ሌሎች አመራሮቹን መምረጡም አይዘነጋም።