Posts

ለመሆኑ ኢትዮጵያ በሃይማኖቶች መከባበር ለኣፍሪካ ምሳሌ ናትን?

Image
የኢትዮጵያ ሃይማኖቶች መከባበር ለአፍሪካ ምሳሌ ነው ተባለ  ምንጭ፦  ኢብኮ Ethiopia Destroys Evangelical Church Building; 100 Christians Forced Underground .  ምንጭ፦  ቦስኒውላይፍ  ሰሞኑን ኢትዮጵያ በሃይማኖቶች መከባበር ለኣፍሪካ ምሳሌ መሆናን በመግለጽ የመንግስት የወሬ ኣውታሮች የዘገቡ ሲሆን፤ በተቃራኒው ደግሞ  በኣገሪቷ የሃይማኖቶች የመቻቻል ባህል ኣደጋ ላይ መሆኑን የምገልጹ ወሬዎች ተሰምቷል። በኢትዮጵያ ባለው የሃይማኖቶች መከባበር ዙሪያ የተነገሩትን ሁለት ፊት ወሬዎችን ከታች ያንቡ፦ መቀመጫውን በደቡብ አፍሪካ ያደረገው አክሽን የድጋፍ ማዕከል የተባለ የሠላም ተቋም ባካሄደው የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ላይ ከአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ የሃይማኖት መሪዎች ተካፋይ ሆነዋል፡፡ የማዕከሉ ስራ አስኪያጅ ፒላኒ ዲዴቤሌ እንዳሉት በኢትዮጵያ ያለው የሃይማኖቶች መከባበር ለአፍሪካ ሀገራትም በምሳሌነት ሊማሩበት የሚገባ ነው፡፡ በመሆኑም  ጉባኤው በአዲስ አ,በባ እንዲካሄድ መደረጉን ነው የተናገሩት፡፡ ፒላኒ ዲዴቤሌ የአፍሪካ ሀገራት ከሠላምና ጸጥታ ባሻገር በሀገር ልማት ሃይማኖቶች እንዴት አስተዋጽኦ ያደርጉ ለሚለው ጥያቄ መልሱን የምናገኘው ከኢትዮጵያ ነው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሃፊ ፓስተር ዘሪሁን ደጉ የዕምነት ተቋማትንና 97 በመቶ ህዝብ ያቀፈው ጉባኤው የሚያደርገው የሠላምና የልማት አስተዋጽኦ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ የሃይማኖት ተቋማት በራሳቸው የሚሰሩት የሠላምና የልማት ተግባርም ለአፍሪካ ሀገራት እንደአህጉር ያለንን የሠላምና ልማት የማረጋገጥ አላማ የሚያግዝ ነው ብለዋል፡፡ በአፍሪካ ህብረት በተካሄደው ጉባኤ የአፍሪካ የህዝብ ለህዝብን መደጋ

Not Just for Export: Ethiopia's Coffee Culture

Image
My first trip to a coffee-producing country was in 2008. I was traveling to Costa Rica, and right up there with surfing in Tamarindo and seeing the Volcan Arenal was what I considered a culinary must: sampling some fabled Costa Rican roast. Imagine my dismay when, upon settling into a cozy local restaurant, and requesting a coffee, I received... Nescafe. As I continued to travel to countries famous for their coffee - Peru, Tanzania, Rwanda - I realized that my experience in Costa Rica was no aberration. As many frustrated travelers come to find, the countries richest in coffee often produce almost exclusively for export, resigning themselves to drinking instant. Not so in Ethiopia. Coffee culture in Ethiopia - considered to be the drink's birthplace - dates back centuries, and continues to this day. In fact, according to the International Coffee Organization (ICO), domestic coffee consumption accounts for  more than half  of the country's production; unheard of in A

የፀረ ሙስና ኮሚሽን በቡና ወጪ ንግድ ችግሮች ላይ ያካሄደው ጥናት መጠናቀቁ ተሰማ

የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በቡና የወጪ ንግድ ላይ በተፈጠሩ ችግሮች ዙሪያ ሲያካሂድ የቆየውን ጥናት ማጠናቀቁን ምንጮች ገለጹ፡፡ ኮሚሽኑ ሕገወጥ ሥራ ሠርተዋል ባላቸው ላይ ዕርምጃ ለመውሰድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጋር እየተነጋገረ መሆኑ ታውቋል፡፡ የፀረ ሙስና ኮሚሽን ረዘም ያለ ጊዜ ወስዶ ሲያካሂድ የቆየው ምርመራዊ ጥናት ተጠያቂ የሚሆኑትን እንደለየ የሚናገሩት ምንጮች፣ በቀጣይነት መወሰድ ባለበት ሕጋዊ ወይም አስተዳደራዊ ዕርምጃ ላይ በከፍተኛ ባለሥልጣናት ደረጃ ውይይት እየተካሄደ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ወዶ አጦ፣ ጥናቱ እየተካሄደ መሆኑን ነገር ግን ገና አለመጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ምንጮች ግን ኮሚሽኑ በንግድ ሚኒስቴርና በቡና ላኪዎች ላይ ትኩረት አድርጎ ሲያካሂድ የቆየውን ጥናት ማጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ ጥናቱ ትኩረት ካደረገባቸው ጉዳዮች መካከል ንግድ ሚኒስቴር በቡና ላኪዎች ላይ በቂ ክትትልና ቁጥጥር አለማድረጉ፣ የተሟላ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት አለመኖሩ፣ በሁሉም ድርጅቶች ላይ ወቅቱን የጠበቀ የቡና ክምችት ቆጠራ አለመካሄዱ፣ ለውጭ ገበያ የተዘጋጀን ቡና ኤክስፖርት በማያደርጉ  ነጋዴዎች ላይ ዕርምጃ አለመወሰዱ፣ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በሚሸጥ የቡና ገለፈት ላይ ተገቢውን ቁጥጥርና ክትትል አለመደረጉ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ከዚህ በላይ ጐልቶ የታየው ችግር ደግሞ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ሳይሰጥ ቡናን ወደ ውጭ አገር ኤክስፖርት ማድረግ ነው፡፡ ብሔራዊ ባንክ ወደ ውጭ ለሚላክ ቡና የሚሰጠው ፈቃድ አለ፡፡ ይህ ፈቃድ ካልተገኘም ቡና ወደ ውጭ መላክ የተከለከለ ነው፡፡ ነገር ግን የተወሰኑ ነጋዴዎች ይህ ፈቃድ ሳይኖራቸው

ሃዋሳ

Image
http://www.diretube.com/walta/a-closer-look-hawassa-city-video_29dadc2b7.html

ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ አለም አቀፍ የቦንድ ሸያጭ ገበያን ዛሬ ትቀላቀላለች

Image
( ኤፍ.ቢ.ሲ ) ኢትዮጵያ ዛሬ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ አለም አቀፍ የቦንድ ሸያጭ ገበያን ትቀላቀላለች ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ለሽያጭ ይቀርባል ተብሎ የሚጠበቀው የቦንድ መጠንም 1 ቢሊየን ዶላር መሆኑ ተነግሯል። አገሪቱ ከቦንድ ሽያጩ አስቀድሞ በአገሪቱ ውስጥ ስላሉ ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታዎችና በምትሸጠው ቦንድ የምታገኘውን ገንዘብም ለምን ለምን ተግባራት ልታውለው እንዳሰበች በአውሮፓና በአሜሪካ ለሚገኙ የገንዘብ አበዳሪ ባለሀብቶች ለአንድ ሳምንት የዘለቀ ገለፃ ስታደርግ ቆይታለች። ይህን ገለፃዋንም ትናንት ለመጨረሻ ጊዜ በአሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ ለሚገኙ ባለሀብቶች በማቅረብ ማጠናቀቋንም ፋይናንሽያል ታይምስ ዘግቧል። በኒውዮርክ ገለፃ ላይ የተገኙት ባለሀብቶችም በአጠቃላይ ኢትዮጵያ እየተጓዘችባቸው ስላሉት ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ተብራርቶላቸዋል። እንደዘገባው ከሆነ በዛሬው ዕለት ጄ ፒ ሞርጋንና ደች ባንክ የኢትዮጵያን ቦንድ ለአለም አቀፍ አበዳሪ ባለሀብቶች ይዘው እንደሚቀርቡ ይጠበቃል። ኢትዮጵያ የተበደረችውን ገንዘብም በ10 ዓመታት ውስጥ የምትመልስ ይሆናል። የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አይ ኤም ኤፍ በዚህ ዓመት ኢኮኖሚያቸው በፍጥነት ይመነደጋል ብል ካስቀመጣቸው አገራት መካከል ኢትዮጵያን በስምንተኛነት አስቀምጧታል። የኢትዮጵያ መንግስት ኢኮኖሚያዊ ዕድገቱን ለማስቀጠል ያለው ቁርጠኝነትም ቦንዱን ለሚገዙ የገንዘብ አበዳሪ ባለሀብቶች አስተማማኝ እፎይታን እንደሚያጎናፅፋቸው ተገምቷል።