Posts

ደመወዛችን ሃምሳ ጉዳያችን መቶ!

እነሆ ከመገናኛ ወደ ሲኤምሲ ልንጓዝ ነው። አጀማመራችን በፀጥታ የተጠነሰሰ ነው። የዛሬዎቹ ተሳፋሪዎች ትንፋሽ ያላቸው አይመስሉም። በውጥረት የታፈነው ጎዳና መንገደኛውን መተንፈሻ የነሳው ይመስላል። ጩኸት ኑሮው የሆነው ወያላ ዕድሜው በለቅሶ ተጀምሮ በጩኸት በሚገባደድ ሕዝብ መሀል ያለ ዕረፍት ይጣራል። እንደ ንጋት ጎርናና ድምፁ ሁሉ ጎርበጥባጣ ኑሮው ይለሰልስለት ይመስል እሪ ሲል አይታክትም። ጥሪ በማይፈልገው የትግል ጎዳናችን ላይ ግን የወያላው ልፋት መና የቀረ ይመስላል። ከወዲያ ወዲህ ሲሯሯጥ ከቆየ በኋላ አካባቢውን የሚቀያይረው ሕዝብ ፍልሰቱ መቼም የሚቆም አይመስልም። ሰው የሚደርስበትን ቦታ እያሰበ ስለአዋዋሉ፣ ስለኑሮው፣ ስለቤተሰቡ፣ ስለሥራው እያውጠነጠነ ባላሰበው በሚገኝበት በዚህ ጊዜ፣ የህልማችንና የሩጫችን ውጤት በአብዛኛው አንገት ያስደፋል። ሲዘሉ መሰበር የመንገዱ ህልውና መሠረት ቢሆንም ቅሉ በዚህ በአገራችን የአረማመድ ዘዬ ሳንዘል በተቀመጥንበት የተሰበርን ጥቂት አይደለንም። የዚህ ጎዳና ትርክት ብዙ ነው።  ማጠቃለያ ሐሳብ ይሰጠው ሲባል ግን ቃሏ አንዲት ናት። እሷም ‘ተግዳሮት’ ትባላለች። መውጣትና መውረድ አክርማና ስንደዶ ሆነው ያልቀየሱት ጎዳና በእርግጥ በየትም አገር ታሪክ አይኖርም። ነፃ ብሎ መንገድ፣ እንደ ጨርቅ የሚጠቀለል አልጋ ባልጋ ጎዳና ለሰው ልጅ አይገባውም የተባለ የተፈጥሮ ሕግ ሳይሆን አይቀርም። በዚህ ግጭቱ፣ ተንኮሉ፣ ተግዳሮቱና ሸሩ በማያልቅ የሰው ልጅ ሕይወት ሁሉም እንደራሱ አረማመድ እየተጓዘ እንደ ሕዝብ ደግሞ በጋራ መጓጓዣ እንዝርቱ ይፈትላል። በፈተለው ልክ ሁሉም የድርሻውን ሕይወት እየሸመነና እየለበሰ፣ ለታሪክና ለታዛቢ በሩን ይከፍታል። መንገድ ሁሉን ይዳኛል። የፍትሕ ያለህ ባዩ ወዮታ ግን እያደር በርትቷል። መቼም

የደመወዝ ማስተካከያ ዝርዝር ይዘት በቅርቡ ይፋ ይሆናል ተባለ፤ የደሞወዝ ጭማሪውን ተከትሎ ሃዋሳን ጨምሮ በኣንዳንድ የሲዳማ ከተሞች በሸቀጦች ላይ የዋጋ ጭማሪ ታይቷል

Image
ለመንግስት ሠራተኛው የተደረገው የደመወዝ ማስተካከያ ዝርዝር ይዘት በመጪዎቹ ሁለት ሣምንታት ይፋ እንደምሆን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። መገናኛ ብዙሃኑ የመንግስት ከፍተኛ የሰራ ሃላፊን ጠቅሰው እንደዘጋቡት፤ መንግስት የሲቪል ሠራተኛውን ኑሮ ለማሻሻል ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የደመወዝ ማስተካከያ በዋነኝነት ተጠቃሽ መሆኑን ነው።  በአሁኑ ወቅት የደመወዝ ማስተካከያው ዝርዝር ሥራ በመከናወን ላይ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፤ በመጪዎቹ ሁለት ሳምንታት ውስጥ ይፋ እንደሚሆን ገልጸዋል። አስፈላጊ ሥራዎች ከተጠናቀቁ የተደረገው የደመወዝ ማስተካከያ ከሐምሌ ወር 2006 ዓ . ም ጀምሮ ለሠራተኛው የሚከፈል መሆኑን ታውቋል ። በተመሳሳይም የመንግስት ሠራተኛውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ እየተገነቡ ካሉት የጋራ መኖሪያ ቤቶች የ 20 በመቶ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ የመንግስት መገናኛ ብዙሃኑ አመልክተዋል። ኣክለውም የሠራተኛውን የትራንስፖርት ችግር ለመቅረፍም በፌዴራል ደረጃ ለዚሁ አገልግሎት የሚውሉ ተሽከርካሪዎች እየተመረቱ መሆኑንና በቅርቡ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ አስረድተዋል። አንዳንድ ነጋዴዎች የደመወዝ ማስተካከያውን ተከትሎ በመሰረታዊ ሸቀጦች ላይ የዋጋ ጭማሪ እንዳያደርጉ መንግስት የተለያዩ የቁጥጥር ሥራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል ብለዋል። በሌላ በኩል መሰረታዊ የሚባሉ ሸቀጦችን በ " አለ በጅምላ " ድርጅት በኩል በማቅረብ ኅብረተሰቡ ሸቀጦችን ፍትሃዊ በሆነ ዋጋ እንዲያገኝ የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱን ጠቅሰዋል። የደመወዝ ማስተካከያው ኢኮኖሚው ተረጋግቶ መቀጠል በሚችልበትና የኑሮ ውድነትን በማያባብስ መልኩ ተጠንቶ ተግባራዊ የሚደረግ እንደሆነም ተ ገልጸዋል። ባለፈው ሰኔ 16 ቀ

High court ruling says UK should respect human rights in Ethiopia

LONDON, July 15 (RIA Novosti) – The UK High Court’s Monday ruling allowing to review the UK aid agency’s compliance with its own human rights policies in Ethiopia signals the need for the British government and other donors to uphold their commitments, Human Rights Watch (HRW) said in a press release. In its July 14 ruling, the High Court said that allegations that the UK Department for International Development (DFID) has failed to adequately assess evidence of human rights violations in the African country deserve a full judicial review. “The UK High Court ruling is just a first step, but it should be a wake-up call for the government and other donors that they need rigorous monitoring to make sure their development programs are upholding their commitments to human rights,” Leslie Lefkow, HRW deputy Africa director, said. The primary human rights violations took place within the “villagization” program, a compulsory resettlement of people into designated villages, which was carried

በኣይነቱ የመጀመሪያ የሆነ እና ሙሉ በሙሉ በሲዳማ ኣፎ የተተርጎመ ፊልም...

The Jesus Film - Sidaama / Sidamo / Sidaamu Afoo / Sidaminya / Sidámo 'A... ስነ ሲኒማ የኣንድን ህዝብ ባህል፤ ታሪክ፤ ሰብዕና፤ ዘዴ_ልማዳዊ ኣኗኗር፤ቱፍት፤ እሴት በኣጠቃላይ ማንነት ለማስቀዋወቅ ያለው ፋይዳ የእትዬሌሌ ነው። በኣሁኑ ጊዜ ከቴክኖሎጂ እድገት ጋር ተያይዞ በዓለማችን ላይ ስነ ሲኒማ የህዝቦችን የእለተ እለት ኣኗኗር በመሸከፍ ህዝቦች በስልጣኔ የደረሱበትን ደረጃ ለመጪው ትውልድ በታሪክ በማስቀረት ላይ ነው። በኣገራችንም ብሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኣቅሚቲ በሚመረቱ ፍልሞች ራሳችንን እና ኣኗኗሯችንን በፊልሞች ማየት ጀምረናል። በዘፈን ክሊፖች እና በቲቪ ላይ ድራማዎች የተጀመረው የኣገራችን ስነ_ሲኒማ ዛሬ ላይ ኤች ዲ ጥራት ወዳላቸው ባለ 35 ሚ/ሜትር ፊልሞች ኣድጓል፤ ምንም እንኳን ኣሁንም ብዙ የምቀረው ቢሆንም። በኢትዮጵያ የሲኒማ ኢንዱስትሪ ላይ በመታየት ላይ ባለው እድገት በዋናነት በኣማርኛ ቋንቋ የምመረቱ የሲኒማ ስራዎች በመበራከት ላይ ሲሆኑ፤ ከኣማርኛ ቋንቋ ቀጥሎ በኦሮሚፋ እና ትግርኛ ቋንቋ የተሰሩ ስራዎች ይበዛሉ። የሲዳማ ኣፎ በኣገሪቱ የሰነ ሲኒማ ኢንዱስትሪ ውስጥ ያለው ቦታ እጅግ በጣም ዝቅተኛ ነው። በሲዳማ ኣፎ የተሰሩ ስነ ሲኒማ ነክ ስራዎች በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። ኣሉም ብባሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ታትመው የወጡትን መንፈሳዊ መዝሙሮች ክሊፖች ካልሆኑ በስተቀር ለላ ስራ ለመጥቀስ ይከብዳል። በርግጥ በሲዳማ ኣፎ የምሰራጭ የቴለቪዥን ጣቢያ ኣለመኖሩ፤ ህዝቡ በራሱ በኣብዛኛው የገጠር ነዋሪ መሆኑ እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ባለበት ኣለመሆን፤ በኣጠቃላይ የሰነ ሲኒማ ባህል ኣለመኖሩ ለሲዳማ ሲኒማ ኢንዱስትሪ ዝቅተኛነት እንደምክንያት ማንሳት ይቻላል። በእነዚህ እና በሌሎች ባልጠቀ

ሲዳማ ያፈራቻቸው ታላላቅ ጸሃፊት:ደራሲ እና ባለቅኔ ደበበ ሰይፉ

Image
“ይርጋለም ዋ… ይርጋለም የልጅነቴ ህልም ቀለም ዓይኔን የከፈትሽው ጨረር ወርቃማይቱ ጀንበር” ብሎ ደበበ ፅፎታል። ደራሲ ደበበ ሰይፉ ፎቶ ከ ኣዲስ ገጽ ሲዳማ በኢትዮጵያ የሰነ ጽሁፍ ታርክ ኣንቱ የተባሉ ጸሃፊትን ኣፍርታለች። በተለይ ኣንጋፋዋ የሲዳማ ከተማ የሆነችው ይርጋዓለም/ ዳሌ በርካታ ደራሲያን እና ጸሃፍት የፈለቁባት ከተማ ናት። ይርጋዓለም ለስነ ጽሁፍ የሚመች ድባብ ኣላት። ነዋሪዎቹዋም ይህንን ደባብ ተጠቅመው የጥበብ ስራዎቻቸውን ለሰነ ጥበብ ኣፍቃሪያን ማድረሳቸውን ተያይዘውታል። “ይርጋለም ዋ… ይርጋለም የልጅነቴ ህልም ቀለም ዓይኔን የከፈትሽው ጨረር ወርቃማይቱ ጀንበር” ብሎ ደበበ ፅፎታል። ምንም እንኳን በሲዳማ ቋንቋ ይህ ነው የምባል የጎላ ስራ ከይርጋዓለም ባይወጣም በኣማርኛ ቋንቋ ግን ኣያሌ ስራዎች ለንባብ በቅተዋል።  የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ይርጋዓለም_ዳሌ በኣገሪቱ ሰነ ጽሁፍ ያላትን ሚና ለመዘከር ኣንጋፋ ጸሃፊቷን ለኣንባቢያን ያስተዋውቃል፤ ለዛሬ ደራሲ እና ባለቅኔ ደበበ ሰይፉ እነሆ ብለናል፦    የደራሲው ሥራዎች 1.    የብርሃን ፍቅር (ግጥምና ቅኔ) 2.    ለራስ የተፃፈ ደብዳቤ (ግጥምና ቅኔ) 3.    ከባሕር የወጣ ዓሣ (ተውኔት) ስለደራሲው በጥቂቱ ደበበ ሰይፉ  የ አማርኛ  ባለቅኔ ነበሩ። ሚያዚያ 16 ቀን 1992 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ደበበ ሰይፉ ዘርፈ ብዙ የጥበብ ሰው ነው፡፡ ገጣሚ፣ ሃያሲ፣ መምህር፣ ጸሐፊ-ተውኔት፣ የሥነ-ጽሑፍ ተመራማሪ… ነው፡፡ “የብርሃን ፍቅር” እና “ለራስ የተጻፈ ደብዳቤ” የግጥም ሥብስቦቹ የተደጎሱባቸው መጻሕፍቱ ናቸው፡፡ ከዚህ ለጥቆ ያለው መረጃ /አቀናባሪ አሉላ ከ EthioCurrent