ሲዳማ ያፈራቻቸው ታላላቅ ጸሃፊት:ደራሲ እና ባለቅኔ ደበበ ሰይፉ
“ይርጋለም ዋ… ይርጋለም የልጅነቴ ህልም ቀለም ዓይኔን የከፈትሽው ጨረር ወርቃማይቱ ጀንበር” ብሎ ደበበ ፅፎታል። ደራሲ ደበበ ሰይፉ ፎቶ ከ ኣዲስ ገጽ ሲዳማ በኢትዮጵያ የሰነ ጽሁፍ ታርክ ኣንቱ የተባሉ ጸሃፊትን ኣፍርታለች። በተለይ ኣንጋፋዋ የሲዳማ ከተማ የሆነችው ይርጋዓለም/ ዳሌ በርካታ ደራሲያን እና ጸሃፍት የፈለቁባት ከተማ ናት። ይርጋዓለም ለስነ ጽሁፍ የሚመች ድባብ ኣላት። ነዋሪዎቹዋም ይህንን ደባብ ተጠቅመው የጥበብ ስራዎቻቸውን ለሰነ ጥበብ ኣፍቃሪያን ማድረሳቸውን ተያይዘውታል። “ይርጋለም ዋ… ይርጋለም የልጅነቴ ህልም ቀለም ዓይኔን የከፈትሽው ጨረር ወርቃማይቱ ጀንበር” ብሎ ደበበ ፅፎታል። ምንም እንኳን በሲዳማ ቋንቋ ይህ ነው የምባል የጎላ ስራ ከይርጋዓለም ባይወጣም በኣማርኛ ቋንቋ ግን ኣያሌ ስራዎች ለንባብ በቅተዋል። የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ይርጋዓለም_ዳሌ በኣገሪቱ ሰነ ጽሁፍ ያላትን ሚና ለመዘከር ኣንጋፋ ጸሃፊቷን ለኣንባቢያን ያስተዋውቃል፤ ለዛሬ ደራሲ እና ባለቅኔ ደበበ ሰይፉ እነሆ ብለናል፦ የደራሲው ሥራዎች 1. የብርሃን ፍቅር (ግጥምና ቅኔ) 2. ለራስ የተፃፈ ደብዳቤ (ግጥምና ቅኔ) 3. ከባሕር የወጣ ዓሣ (ተውኔት) ስለደራሲው በጥቂቱ ደበበ ሰይፉ የ አማርኛ ባለቅኔ ነበሩ። ሚያዚያ 16 ቀን 1992 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ደበበ ሰይፉ ዘርፈ ብዙ የጥበብ ሰው ነው፡፡ ገጣሚ፣ ሃያሲ፣ መምህር፣ ጸሐፊ-ተውኔት፣ የሥነ-ጽሑፍ ተመራማሪ… ነው፡፡ “የብርሃን ፍቅር” እና “ለራስ የተጻፈ ደብዳቤ” የግጥም ሥብስቦቹ የተደጎሱባቸው መጻሕፍቱ ናቸው፡፡ ከዚህ ለጥቆ ያለው መረጃ /አቀናባሪ አሉላ ከ EthioCurrent