Posts

የኮሪያ መንግሥት ለሞጆ-ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ የፈቀደው ብድር ለፓርላማ ቀረበ

ከሞጆ-ሐዋሳ የመጀመሪያ ዙር የፍጥነት መንገድ ግንባታ የኮሪያ መንግሥት ኤግዚም ባንክ የፈቀደው 100 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለፓርላማ ቀረበ፡፡ የሞጆ-ሐዋሳ መንገድ 201 ኪሎ ሜትር ርዝመት ሲኖረው፣ ግንባታው በሁለት ዙር ተከፍሎ የሚገነባ ነው፡፡ የጀመሪያው ዙር ግንባታ ከሞጆ-ዝዋይ በራሱ በሁለት ተከፍሎ የሚገነባ መሆኑን የብድር ማፅደቂያ አዋጁ አባሪ ሰነድ ያብራራል፡፡ የመጀመርያው ዙር የመጀመርያ ምዕራፍ ከሞጆ-መቂ ሲሆን፣ ለዚህ ግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውል 128 ሚሊዮን 460 ሺሕ ዶላር በዚህ ዓመት ከአፍሪካ ልማት ባንክ መገኘቱን ሰነዱ ያብራራል፡፡ ለቀሪው የመቂ-ዝዋይ መንገድ ግንባታ ደግሞ የኮሪያ ኤክስፖርት ኢምፖርት (ኤግዚም) ባንክ 100 ሚሊዮን ዶላር መፈረሙን የአዋጁ አባሪ ይገልጻል፡፡ ከሞጆ-ሐዋሳ ድረስ የሚገነባው የፍጥነት መንገድ በአንድ ጊዜ አራት ተሽከርካሪዎችን እንዲያስተናግድ ይፈለጋል፡፡ አጠቃላይ ወጪውም 349 ሚሊዮን 480 ሺሕ ዶላር መሆኑን ሰነዱ ይገልጻል፡፡  ከኮሪያ መንግሥት የተገኘው 100 ሚሊዮን ዶላር የ15 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ጊዜ ውስጥ ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ለፕሮጀክቱ ትግበራ ባንኩ በሚፈጽመው ክፍያ ላይ 0.1 በመቶ የአገልግሎት ክፍያ ከብድሩ ገንዘብ ላይ ተቀንሶ እንደሚከፈል፣ ጥቅም ላይ ባልዋለውና ባልተከፈለው የብድር ገንዘብ ላይ ደግሞ 0.01 በመቶ ወለድ እንደሚታሰብበት ረቂቅ ማፅደቂያ አዋጁ ይገልጻል፡፡ የብድር ስምምነቱ እስከዛሬ ከነበሩት የብድር ዓይነቶች ጋር ሲነፃፀር የ55 ዓመት መሆኑ፣ የአገልግሎት ክፍያውና ወለዱ በጣም ዝቅተኛ መሆኑ የፓርላማው አባላትን አስደንቋል፡፡ ‹‹የኮሪያ ኤግዚም ባንክ ብድር ሳይሆን ስጦታ ነው የሰጠው፤›› ሲሉ የምክር ቤቱ ዶ/ር አድሃና ኃይሌ አድንቀውታ

የኢትዮጵያ ሴቶች እግር ኳስ ፕሪሚየር ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ነገ በሀዋሳ ከተማ ይጀመራል

Image
የሲዳማ ቡና የሴቶች ብድን ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም በሚካሄደው በዚህ ጨዋታ ተወዳዳሪ ክለቦች፣ የውድድር ባለሙያዎች ደጋፊዎችና ሌሎች እንግዶች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ዜና ኣገልግሎት እንደዘጋበው፤ ለፍጻሜ ውድድር በወጣው ደንብ መሰረት ሀዋሳ ከነማና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የየምደቡ አሸናፊ በመሆናቸው የምድብ አንድና ሁለት አባትነት ደረጃ ሲያገኙ የቀሩት ክለቦች ግን በደረጃቸው መሰረት ድልድል ይደረግላቸዋል። ከ2ኛ እስከ 4ኛ ደረጃ ባለው የምድብ ተራ ቁጥር ያሉት ደግሞ በዕጣ የሚወሰኑ ይሆናል። ከየምደቡ አንደኛና ሁለተኛ የሚወጡት ቡድኖች ለጥሎ ማለፍ ውደድር የሚያልፉ ሲሆን ተሸናፊዎች ለሶስተኛ ደረጃ፣ አሸናፊዎች ደግሞ ለዋንጫ ፍልሚያ የሚያደርጉ ይሆናል። ቀደም ሲል ባስመዘገቡት ውጤት መሰረት ከማዕከላዊ ሰሜን ዞን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ደደቢት፣ ቅዱስ ጊዮርጊስና ዳሽን ቢራ ሲገኙ ከደቡብ ምስራቅ ዞን ደግሞ ሀዋሳ ከነማ፣ ሲዳማ ቡና፣ አርባ ምንጭና ድሬድዋ ከተማ ለፍፃሜ ውድድር ያለፉ ናቸው። ሀዋሳ ጨዋታውን ለማካሄድ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጓንና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽንም ውድድሩ የተሳካና ያማረ እንዲሆን አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማደረጉን ገልጿል። ፈዴሬሽኑ ለሸናፊዎቹ የዋንጫና የሜዳሊያ ሽልማት እንዲሁም ለኮከብ ተጫዋቾች፣ ለአሰልጣኞችና ለዳኞች የማበረታቻ ሽልማት እንደሚያደርግ ማሰታወቁን ኢዜኣ ዘግቧል።

የመንግስት መገናኛ ብዙሃን የሲኣን/ መድረክ ሰላማዊ ሰልፍ ተሳታፊዎችን ቁጥር ኣሳንሰው ዘገቡ

Image
ከሰላማዊ ሰልፈኞቹ መካከል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን በዛሬው እለት በሃዋሳ ከተማ የተካሄደውን የሲኣን/ መድረክ ሰላማዊ ሰልፍ ተሳታፊዎችን ቁጥር በእጅጉ ኣሳንሰው መዘገባቸው ተሰማ። በወቅታዊው የኣገሪቱ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ድምጻቸውን ለማሰማት ወደ ኣደባባይ በርካታ ቁጥር ያለው ህዝብ የተመመ ሲሆን፤ በሰላማዊ ሰልፉ ላይ በሺዎች የምቆጠሩ ሰዎች መገኘታቸውን ከሲኣን የተገኘው መረጃ ያመክታል። ሆኖም የመንግስት መገናኛ ብዙሃን  ይህንን ብዛት የለውን ሰላማዊ ሰልፈኛን ቁጥር በማሳነሰ የሰላማዊ ሰልፈኛውን ቁጥር ወደ 200 ኣውርደው መዘገባቸው ታውቋል። ከመገናኛ ብዙሃኑ ዘጋባ መካከል የሚከተለውን ለኣብነት ኣቅርበነዋል፦  መድረክ በሀዋሳ ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ አካሄደ ሀዋሳ ሰኔ 07/2006 የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ዛሬ በሀዋሳ ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ አካሄደ፡፡ መድረክ በዚሁ ሰልፍ ላይ የተለያዩ የተቃውሞ መፈክሮችን አሰምቷል፡፡ የመድረክ ዋና ጸሐፊ አቶ ገብሩ ገብረማርያም በሰልፉ ላይ እንዳሉት ኢህአዴግ የህግ የበላይነትን በማክበርና በማረጋገጥ ነጻ ፍትሐዊ ዴሞክራሲያዊና ታዓማኒነት ያለው ገለልተኛ የምርጫ አስተዳደር እውን እንዲሆን ማድረግ አለበት፡፡ ዜጎች ያለ ፖለቲካዊ ወገንተኝነት ከሀገራቸው ልማትና እድገት ውጤቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንጠይቃለን ብለዋል። መድረክ የሀገሪቱን ወቅታዊና መሰረታዊ ችግሮች መፍቻ አቅጣጫ ነው ያለውን ማንፌስቶ በህዝቡ ድጋፍ ስራ ላይ እንዲውል ለማድረግ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጿል፡፡ በሰልፉ ላይ የተሳተፉት ሰዎች  ከ200 በላይ እንደሚገመቱ በስፍራው የነበሩ የአይን እማኞች ገልጸዋል፡፡ ሰልፉም በሰላም መጠናቀቁን ጸጥታ አንዳንድ የጸጥታ አስከባሪዎች ተናግረዋል፡፡

ሲኣን/ መድረክ የጠራው ታላቅ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ በሃዋሳ ከተማ ተካሄደ

Image
ዛሬ ከቀኑ ሶስት ሰዓት ላይ ከወልደኣማኑኤል ዱባሌ ሐውልት የተሰባሰበው ሰላማዊ ሰልፈኛ በኣቶቴ እንድሁም በየሙሉ ወንጌል በተክርስቲያን በኩል ኣድርጎ ወደ መናሃሪያ በመትመም መጨረሻውን ከሃዋሳ መስቀል ኣደባባይ ኣድርጓል። ሪፖተራችን ጥቻ ወራና እንደዘጋበው በሰላማዊ ሰልፉ ላይ በሺዎች የምቆጠሩ ሰዎች የተገኙ ሲሆን የፖለቲካ እና የህሊና እስረኞች ይፈቱ፤ በልማት ስም ህዝብን ማንገላታት ይቁም፤ የኣገራችን የፖለቲካ ችግሮች በድርድር እንጂ በኃይል ኣይፈቱም የምሉ መፎክሮችን ኣስምተዋል። በሰልፉ ላይ ተጋባዥ እንግዶችን እና የመድረክ /   ሲኣን ከፍተኛ ኣመራሮች ተገኝተው ለህዝብ የተለያዩ መልዕክቶችን ያስተላለፉ ሲሆን፤ ሰላማዊ ሰልፉ በፍጽም ሰላማዊ መሆነ ሁኔታ ያለምንም ችግር መጠናቀቁን ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና ከሃዋሳ ዘግቧል። 

We floated a tender for the construction of the Hawassa and Robe Airports: The Ethiopian Airports Enterprise

Image
Wondeme Teklu, head of the communication affairs office at the Enterprise. Source  addisfortune.net Jinka Airport Given Green Light With Construction Contract The Ethiopian Airports Enterprise is also looking to construct new airports in Hawassa and Robe The Ethiopian Airports Enterprise (EAE) has awarded a 571.7 million Br contract to Afro-Tsion Construction Plc for the construction of the country’s 18th airport at Jinka, 587kms south of Addis Abeba. The Enterprise contracted the project to Afro-Tsion on May 27, 2014, and the contractor was handed over the land, located three kilometres away from Jinka town, on Thursday June 5, 2014. Afro Tsion, a grade one general contractor, was established in 1990 and is engaged in road and bridge construction, infrastructure and real estate development and water works. The contractor has previously worked on the construction of numerous projects, such as Mekele University, Oromia Regional Offices, Gondar University, Assela Mal