Posts

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት 2ኛውን የኦፕን ዶር(Open-Door) ቀን አከበረ

Image
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እና የደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ/መ ንግድ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ በጋር በመሆን ሁለተኛውን የኦፕን ዶር ቀን በደመቀ ሁኔታ ሚያዝያ 14/2006 ዓ.ም አከበሩ፡፡ "የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስር ለህዳሴያችን" በሚል መሪ ቃል በተከበረው በዓል ላይ የፕሬዚዳንት ጽ/ቤትን በመወከል ዶ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ የመክፈቻ ንግግር አድረገዋል፡፡ እሳቸው እንዳሉት ኦፕን ዶር በሀገራችን ብዙም ያተለመደ ነገር ግን የተለያዩ የምርምርና የቴክሎጂ ውጤቶችን የምናስተዋውቅበት ዘርፈ ብዙ ጠቃሜታዎች አሉት ብለዋል፡፡ ዶ/ር ፍቅሬ አክለውም ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጂው ዘርፍ እምርታና ለውጥ ለማምጣት ዩኒቨርሲቲው ከአውሮፓ ከካናዳ እና አሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ተባብሮ እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ ዶ/ር ሞልቶት ዘውዴ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር በበኩላቸው እንዳተናገሩት መድረኩ በዩኒቨርሲቲውና እና በኢንስዲስትሪው መካከል ከፍተኛ ትስስር የሚፈጠርበትና ኢንስቲትዩቱ የሚሰራቸውን ስራዎች የምናስተዋውቅበት ነው ብለዋል፡፡ ዶ/ር ሞልቶት አክለው ይህ ቀን እንዲከበር በገንዘብና በተለያዩ ቁሳቁሶች ዩኒቨርሲቲውን የደገፈው የክልሉ ንግድ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮን አመስግነዋል፡፡ ለግማሽ ቀን በዩኒቨርሲቲው የስልጠና ማዕከል በተካሄደው መድረክ በኢንስቲትዩቱ ስር የሚገኙ የትምርት ክፍሎችና ት/ት ቤቶች እያከናወኗቸው ያሉትን ተግባርና እንቅስቃሴ አስተዋውቀዋል፡፡ በመቀጠልም የዩኒቨርሲቲ ኢንዱስትሪ ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችል የመወያያ ሰነድ በዶ/ር ሞልቶት ዘውዴ ቀርቧል፡፡ ውይይቱንም የደቡብ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የክልሉ ንግድ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት

ስለ ሃዋሣ እና ዣ – ን – ዣ – ድ … ባ – ር

Image
ስለ ሃዋሣ እና ዣ – ን – ዣ – ድ … ባ – ር እግር ጥሎኝ… ውበትና ተፈጥሮን አድሎኝ… በፍቅርና በሃሴት ተፍነክነክ ብሎኝ… ደልቶኝ… ሞቆኝ… ምችት፣ ምችትችት ብሎኝ… የሐዋሳ ሰማይ ስር ከርሜ ነበር :: ሐዋሳ ፍቅር እንደሆነች ባየኋት ልክ የምታስደስተኝ… በኖርኩባት ልክ የምትናፍቀኝ… በሸሸኋት ልክ የምታስጨንቀኝ… መሽቶ በነጋ ቁጥር ነገን የምታስመኘኝ የስስት ከተማዬ ናት :: አይደለም አሁን እንዲህ በአስፋልትና በውስጥ ለውስጥ የኮብል ስቶን ንጣፍ አሸብርቃ ይቅርና አቧራ እየለበስን፣ በጠራራ ፀሃይ እየተጠበስን፣ የሞላልን ቀን በጋሪ፣ ያልሞላልን ቀን በኮቴ አሸዋውን በሲሊፐራችን እየዛቅን ስናዘግም እንኳ ለፍቅሯ ጥግ አልነበረኝም… ያን ደማቅ ሰማያዊ የታቦር ሃይስኩል ዩኒፎርም ራሳችን ላይ ጣል እንዳደረግን ጀላቲ እየመጠጥን… አሊያም ሸንኮራ እየጋጥን… ሲደላንም የማዘር ቤትን የ 60 ሳንቲም አምባሻ እየጎመጥን… በላዩ ውሃችንን አንዳንዴም ʿ ሴሏችንን ʾ እየጨለጥን ጎዳናውን ስንሸከሽከው እንኳ ለፍቅሯ ልክ አልነበረኝም… እንዲህ እንደዛሬው በባጃጅ ሽር በሚባልበት ወቅት ይቅርና የጡረታ ዘመኗ ባለፈባት ድክሞ ሳይክል SOS ን አልፌ ጥቁር ዉሃ ድረስ ስንተፋተፍ እንኳ ለፍቅሯ የሚያህላት አልነበረኝም !… ዛሬም የሰላምና የደስታ ጥጌ ሐዋሳ ናት !… ሐዋሳ ሰላም… ሐዋሳ ፍቅር !… እናም የሲዳማን የቆጮ ምግቦችና የወተት አይነቶች እያጣጣምኩ፣ የቶኪቻውን ( የዮሐንስ በቀለን ) ጫምባላላ እየዘፈንኩ ሐዋሳ ከርሜ ነበር… ምንም እንኳ በዛ ያሉ የጭፈራ ዘፈኖች ቢኖሩም ጫምባላላን ግን እጅግ እወደዋለሁ… ከባህል አንፃር ደህና ትርጉም ስላለው ይሆን ?!… ነሸጥ ስለሚያደርገኝ ይሆን ?!… እንጃ ብቻ !… “ አይዴ ጫምባላላ” … “አይዴ ጫምባላላ” … ማ