Posts

በዩኒቨርስቲዎች በተነሳው ተቃውሞ በርካቶች ሞቱ

Image
የከፋ ጉዳት የደረሰው በአምቦ፣መደወላቦ እና ሐረማያ ነው ተቃውሞው እስከ ሃሙስ በመንግስት ሚዲያ አልተነገረም አዲስ አበባንና በዙሪያዋ የኦሮሚያ ከተሞችን በማካተት የተዘጋጀውን የጋራ ማስተር ፕላን የሚያወግዙ የክልሉ ተማሪዎች፤ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ሲያካሂዱት በሰነበቱት ተቃውሞ በሳምንቱ አጋማሽ ላይ ከፖሊስ ጋር በተፈጠረ ግጭት የበርካታ ሰዎች ህይወት ጠፋ፡፡ በትንሹ ወደ መቶ የሚጠጉ ሰዎችም እንደቆሰሉና ጉዳት እንደደረሰባቸው ታውቋል፡፡ በተቃውሞዎቹ ዙሪያ ቀጥተኛ ዘገባ ሲያስተላልፍ የነበረው የመንግስት ሚዲያ ሐሙስ እለት ከመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጽ/ቤት የወጣውን መግለጫ ያቀረበ ሲሆን በአምቦና በመደወላቡ 3 ተማሪዎችን ጨምሮ 7 ሰዎች እንደሞቱ አትቷል፡፡ ሲኤንኤንና ሌሎች የሚዲያ ተቋማት በርካታ ሰዎች መሞታቸውን በመጥቀስ የተለያዩ ዘገባዎችን ያሰራጩ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪዎች ወደ 30 ሰው መሞቱን እንደተናገሩ ጠቅሰዋል፡፡ የእግር ኳስ ጨዋታ በቴሌቭዥን የሚመለከቱ የሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ በተወረወረ ፈንጂ አንድ ተማሪ እንደሞተና 70 ሰዎች እንደቆሰሉም መግለጫው አስታውሶ፤ ዩኒቨርስቲዎች እንደተረጋጉ መንግስት ቢገልፅም በስልክ ያነጋገርናቸው የዪኒቨርሲቲ ተማሪዎችና መምህራን ግን ግጭቱና ውጥረቱ እንዳልበረደ ተናግረዋል፡፡  በአዳማ፣ በጅማ፣ ሃሮማያ፣ አምቦ፣ ነቀምት፣ መደወላቡ እና ድሬደዋ ዩኒቨርሲዎች በተነሳው ተቃውሞ እስካሁን ከተገለጸው በላይ የሞትና የአካል ጉዳት በተማሪዎች ላይ እንደደረሰ የየአካባቢው ምንጮች የገለፁ ሲሂን፣ በርካቶች እንደታሰሩም ጠቁመዋል፡፡ በሃሮማያ ፍንዳታ የሞቱት ተማሪዎች ሁለት መሆናቸውን የገለፁ ምንጮች፣ በብሄር ተወላጅነት የተቧደኑ ተማሪዎች ጎራ ለይተው በፈጠሩት ግጭት በርካታ ተማሪዎች እንደተደባደቡ ተናግረዋል፡፡  አዲስ

Ambo Ethiopia Police Open Fire on Protesters

Ethiopian Music - Teferi - Limbo - Sidama (Official Music Video)

BBC World News reports on Oromo Protest against Addis Ababa Master Plan

“..የነበራት ባልም ይፈታታል... ሌላ ባልም...”

Image
ፎቶ ከ http://kwekudee-tripdownmemorylane.blogspot.com/2013/08/sidama-people-ethiopias-kushitic-expert.html “...እስከአሁን የማልረሳው አንድ አጋጣሚ አለኝ፡፡ አንዲት እናት በቤትዋ ሳለች ምጥ ጀምሮአታል፡፡ ከዚያም ይበልጥ ስትታመምባቸው እኔ ወዳለሁበት በሲዳማ ዞን ቦና ዙሪያ ወረዳ ባለው የጤና ጣቢያ ያመጡአታል፡፡ እኔም ስመለከታት የማህጸን መተርተር ደርሶባታል፡፡ አጋጥሞኝ ስለማያውቅ እጅግ በጣም ነበር የደነገጥኩት፡፡ በእርግጥ በኦፕራሲዮን ማህጸንዋ ይወጣል። ነገር ግን እሱም እርምጃ ቢወሰድ እና ሕይወቷ ቢተርፍ ማህጸንዋ ሲወጣ ወደፊት ልጅ መውለድ ስለማትችል ባለችበት ሕብረተሰብ አስተሳሰብ የምትገለል ትሆናለች፡፡ ምክንያቱም ልጅ ለወደፊቱ መውለድ ስለማትችል የነበራት ባልም ይፈታታል... ሌላ ባልም አያገባትም፡፡ በህብረተሰቡም ዘንድ ተቀባይነት ስለማይኖራት ዝም ብላ የምትኖር ትሆናለች፡፡ይሄንን ነገር ዛሬ ላይ ሳስበው ይቆጨኛል፡፡ ምክንያቱም እንደአሁኑ እውቀቱ ቢኖረኝ ኖሮ ወደከፍተኛ ሕክምና ጊዜ ሳልፈጅ አስተላልፌ በሴትየዋ ላይ የደረሰው ችግር ሊቃለል ይችል ነበር…”  ከላይ ያነበባችሁት ገጠመኝ ከአንድ የጤና መኮንን የቀረበ ነው፡፡ የጤና መኮንኑን ያገኘነው በሐዋሳ በኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር እና በዞኑ የጤና መምሪያ እንዲሁም በፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ትብብር WATCH (women & their child health) የእናቶችና ሕጻናት ጤናን ለማሻሻል በተነደፈው ፕሮጀክት ድጋፍ ስልጠና ሲወስድ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር WATCH (women & their child health) የተሰኘው ፕሮጀክት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ቢንያም ጌታቸው እን