Posts

2ኛው ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬና ነገ ይካሄዳል፤ ሃዋሳ ከነማ ከመብራት፧ ሲዳማ ቡና ከመከላከያ ይጫወታሉ

Image
2ኛው ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬና ነገ ይካሄዳል፤ ሃዋሳ ከነማ ከመብራት፧ ሲዳማ ቡና ከመከላከያ ይጫወታሉ መልካም እድል ለሲዳማ ክላቦች አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 4 ፣ 2006 ( ኤፍ.ቢ.ሲ. ) ሁለተኛው ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬና ነገ ይካሄዳል። ዛሬ ወላይታ ዲቻ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 9 ሰዓት ላይ ሲገናኙ ፤ መብራት ሃይል ከሃዋሳ ከነማ በ11 ሰዓት ከ30 ላይ ይጫወታሉ። ነገ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሙገር በአዲስ አበባ ስታዲየም 10 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ። አርባ ምንጭ ከነማ ከኢትዮጵያ መድህን ፣ ሲዳማ ቡና ከመከላከያ ፣ ዳሽን ቢራ ከሃረር ቢራ በተመሳሳይ 9 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። በሌላ በኩል ሊጠናቀቅ  አምስት ሳምንታት በቀረው በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ስቶክ ሲቲ ከኒውካስትል ፣ ስንደርላንድ ከኤቨርተን ፣ ዌስት ብሮም ከቶተንሃም በተመሳሳይ 11 ሰዓት 07 ላይ ይገናኛሉ። ነገ የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ሁለት ተስተካካይ ጨዋታ ካለውና በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በሶስተኛነት ከተቀመጠው ማንቸስተር ሲቲ ጋር 9 ሰዓት ከ37 ላይ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ቸልሲ በበኩሉ ከሜዳው ውጭ ስዋንሲን 12 ሰዓት ከ07 ላይ ይገጥማል። በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ አርሰናል ከዊጋን አትሌቲክ ምሽት 1 ሰዓት ከ07 ላይ ጨዋታውን  ያደርጋል። በፕሪሚየር ሊጉና በኤፍ ኤ ካፕ ጨዋታዎች የተጨመረው 7 ደቂቃ ፥ ከሃያ አራት አመታት በፊት ሊቨርፑል ከኖቲንግሃም ፎረስት ሲጫወቱ የደረሰውን የሂልስ ቦሮውን አደጋ ለማስታወስ መሆኑ ተገልጿል። በ33ተኛው ሳምንት የስፔን ላሊጋ ዛሬ ግራናዳ ከባርሴሎና 3 ሰዓት ላይ ሲገናኙ ፤ ሪያል ማድሪድ ከአልሜሪያ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።

Ethiopia’s coffee industry booms

Image
Since late last year, a severe drought has stunted growth on coffee plantations in the heart of Brazil’s coffee-growing region and this is reportedly stimulating a resurgence in the Ethiopian coffee industry, whose value has risen to an astonishing 17.5% in one week. Reports indicate that demand for Ethiopian coffee has risen sharply with exporters inking deals worth millions of dollars/pounds. Just two months ago, a pound of exportable washed coffee was traded on the Ethiopian Commodity Exchange (ECX) for 1.15 dollars/pound(0.45kgs). Despite being renowned to be one of the world’s best sources of coffee, a  study  has revealed that only a meagre 1% of Ethiopia’s coffee is sold as specialty. After the drought in the coffee producing belt of Brazil, the price of coffee in the market has shown an increase of 32.5 pc in a matter of 20 days, according to ICE. This drought, which has been described as ‘historic’, has forced more than 140 cities in Brazil to ration water. Rep

መከላከያ ሚኒስቴር የሠራዊቱን ወቅታዊ የብሔር ተዋጽኦ ለፓርላማ ይፋ አደረገ፤ ሲዳማን እና ወላይታን በብዛት የያዘው ደቡብ ሁለተኛ ደረጃ ይዟል

Image
ሰሞኑን የመከላከያ ሚኒስቴር የሰራዊቱን ወቅታዊ የብሄር ተዋጽኦ ለፓርላማ ይፋ ያደረገ ሲሆን ለዘመናት በሰራዊቱ ውስጥ በቁጥርም በጥራትም የበላይነት እንደያዘ የሚነገርለት የትግራይ ክልል በኣማራ ክልል የተተካ መሆኑን ታውቋል። በደቡቦች በመመራት ላይ በሚገኘው መከላከያ ሚኒስቴር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሰራዊቱ የደቡብ ክልል በቁጥር እያደገ የመጣ ሲሆን፤ በብዛት ሲዳማን እና ወላይታን እንደያዘ የተገመተው የደቡብ ክልል በኣሁኑ ጊዜ በብዛት ሁለተኛ ደረጃ ይዟል።  ለዝርዝር ዜናው ከስር ይመልከቱ፦ foto ከድረገጽ Ethiopian reporter በሕገ መንግሥቱ በተደነገገው መሠረት የአገር መከላከያ ሠራዊት የብሔር ተዋጽኦን ለማመጣጠን እየሠራ መሆኑንና በአሁኑ ወቅትም የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ውክልና በሁለተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይፋ አደረጉ፡፡  ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ ባለፈው ሳምንት የመከላከያ ሚኒስቴርን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ለፓርላማው ባቀረቡበት ወቅት ነው የሠራዊቱ የብሔር ተዋጽኦ እየተመጣጠነ መምጣቱን የገለጹት፡፡   በሚኒስትሩ ሪፖርት መሠረት ከአጠቃላይ የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት የአማራ ብሔር ተዋጽኦ 30.3 በመቶ በመሆን ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ በአንደኛነት ሲመራ የቆየ ሲሆን፣ በ2006 ዓ.ም. 29.46 በመቶ በመሆን በቀዳሚነት እየመራ ይገኛል፡፡ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ተዋጽኦ ደግሞ በ2006 ዓ.ም. 25.05 በመቶ በመሆን በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በሪፖርቱ ተመልክቷል፡፡ የኦሮሞ ብሔር በ2004 ዓ.ም. በ25.2 በመቶ የሁለተኛነት ድርሻ ይዞ የነበረ መሆኑን፣ በ2006 ዓ.ም. ግን ወደ 24.45 በመቶ በመውረድ የሦስተኛ ደረጃን እ

የመብት ጥያቄ ያነሱት የሲዳማ ተማሪዎች በኣሸባሪነት ልከሰሱ መሆኑ ተሰማ፤ገዥው ፓርቲ ከተማሪዎቹ ንቅናቄ ጀርባ የሲኣን እጅ ኣለበት በማለት ላይ ነው

Image
ባለፈው ሳምንት በሃዋሳ ከተማ በኣላሙራ እና በታቦር ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የምማሩ የሲዳማ ተማሪዎች በየትምህርት ቤቶቹ ለሲዳምኛ ቋንቋ ትኩረት ተነፍጎታል በማለት ሲዳምኛ ቋንቋ በትምህርት ቤቶቹ የሰራ ቋንቋ መሆን ኣለበት በምል እና ሌሎች የመብት ጥያቄዎችን ኣክለው ድምጻቸውን ባሰሙ ተማሪዎች እና በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች በማካከል በተፈጠረው ግጭት የታሰሩት ተማሪዎች በኣሽባርነት ለመክሰስ መንግስት እየተዘጋጀ ነው። ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና ከሃዋሳ እንደዘጋበው ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ እና በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ተበታትነው ታስረው ከሚገኙት ተማሪዎች መካከል 25 ቱን በኣሸባሪነት ለመክሰስ ኣቃቤ ህግ መረጃ በማሰባሰብ ላይ መሆኑ ታውቋል። በጉዳዩ ጋር በተያያዘ የከተማው ኣስተዳደር የተማሪዎቹን ቤተሰቦች ባለፈው ቅዳሜ ለማናገር የሞከረ ሲሆን፤ በሰብሰባው ላይ የተገኙት የተማሪዎቹ ቤተሰቦች መንግስት በህጻናቱ ላይ የኃይል እርምጃ ከወሰደ በኃላ ልጆቻችሁን ምከሩ የምል መልዕክት ማስተላለፉ የሲዳማን ባህል ያልተከተለ መሆኑን በመግለጽ ቁጣቸውን ኣሰምቷል። እንደተማሪዎቹ ቤተሰቦች ከሆነ፤ በሲዳማ ባህል መሰረት ልጆች ካጠፉ ለወላጆቻቸው ተነግሮ ወላጆቻቸው እንድመክሯቸው ይደረጋል እንጅ የኃይል እርምጃ በመውሰድ በልጆቹ ላይ ጉዳት ካደረሱ በኃላ ምክሩ ማለት ኣግባብነት የለው ብለዋል። በተያያዘ ዜና ከተማሪዎቹ ንቅናቄ ጀርባ የሲኣን / መድረክ እጅ ኣለበት በማለት የገዥው ፓርቲ የተማሪዎቹን ንቅናቄ ፖለቲካዊ ገጽታ በመስጠት ላይ ነው። እንደሪፖተራችን ጥቻ ወራና ገለጻ ከሆነ፤ ገዥው ፓርቲ የተማሪዎቹን የመብት ጥያቄ በኣግባቡ ከመመለሰ ይልቅ ንቅናቄውን ፖለቲካዊ ገጽታ በማላበስ ሲኣንን የመሳሰሉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች

የሀዋሳ መስፋፋትና የሲዳማ ህዝብ ፈተና

Image
ከማህበራዊ መረብ ላይ የተገኘ ጽሁፍ ተጻፈ በደሳለኝ መሳ  ምንጭ፦  Desalegne Mesa ከቅርብ ዓመታት (1950ዎቹ) ወዲህ ከተመሰረተቱት ከተሞች አንፃር ሐዋሳ ጥሩ የሚባል እድገት ጎዳና ላይ እንዳለች የሚታወቅ እውነታ ነው፡፡ በተለይም ተፈጥሮ በለገሰቻት ውበት ምክንያት ሁሉም ሰው ለማለት በሚያስችል መልኩ ልቡ ወደ ሀዋሳ ሽፍተዋል፡፡ ነጋዴዎች ፣ ጎብኝዎች የመንግሥትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ምርጫና መሰብሰቢያ አየሆነች መታለች አዳሬ-ሐዋሳ፡፡ ይህንን የህዝብ ፍልሰትንና ፍላጎት ለማስተናገድና ለማርካት ይመስላል የተለያዩ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች(የማን ናቸው?) መበራከት ጀምረዋል፡፡ የተጠቀሱት ሁሉ የከተማዋን ተጨማሪ ውበት ስለምሰጡ ጥሩ ናቸው፡፡ ከዚህም ያለፈ የተለያዩ ፀሐፊዎች ስለ ሀዋሳ ውበት፣ ሳቢነት፣ ሳብነቱን ተከተሎ እየተከሰቱ ያሉትን ወጣ ያሉ ተግባራትንና የሀዋሳ ሂሊውና የሆነው የሀዋሳ ሀይቅ ብክለትና ስለተደቀነበት ፈተና ጽፈዋል፤ ለሚመለከታቸው ይጠቅማል ያሉትን አስተያየቶችንም ለመሰንዘር ጥረት አድርገዋል፤ የሚሰማ ከተገኘ፡፡ ነገር ግን የዚህ ፅሑፍ አዘጋጅ ትኩረት ለመስጠት የሚፈልገው የከተማውን ያልተጠና መስፋፋትን ተከትሎ እተጎዳ ስላለው ህብረተሰብና ስለተደቀነበት አደጋ ይሆናል፡፡  ከላይ የተጠቀሱት የከተማይቱ መሳጭ ጎኖች ቢኖሩትም በዛው ልክ ደግሞ የህዝብ መከራ የሚያበዙ፣ ከአካባቢ ወጣ ያሉና የምዕራባውያን ባህል መበራከትና ነባሩን የአካባቢውን ባህልና ትውፍት በመዋጥ ረገድ ከፍተኛ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራሉ፡፡ ይህ ወጣ ያለ ነገር እንዳይከሰት ለህዝብና ባህሉ የሚቆረቆር ስርዓት መገንባትና ስርዓቱን የሚመሩ ሰዎችም የአካባቢውን ባህልና ትውፍት በሰለጠነ መልኩ ለጎብኝዎችና ለአዲስ ከታሚ ህዝብ በማቅረብ የባእድ