ገዥው ፓርቲ ሲኣን/መድረክ በሃዋሳ ከተማ የጠራውን ህዝባዊ ስብሰባ ለማደናቀፍ ያደረው ጥረት ሳይሳካ መቅረቱ ተሰማ
ሲኣን / መድረክ ባለፈው ሳምንት በሃዋሳ ከተማ የፖለቲካ ፕሮግራሙን ለኣባላቱ እና ለደጋፊዎቹ ለማስተዋወቅ የጠራውን ህዝባዊ ስብሰባ ገዥው ፓርቲ የመሰብሰቢያ ኣዳራሽ በመከልከል እና የሲኣን / መድረክ ኣባላት በስብሰባው ላይ እንዳይሳተፉ ተጽዕኖ በማድረግ ለማድናቀፍ ያደረጋው ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል። ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና ከሃዋሳ እንደዘጋበው የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ከመድረክ ጋር በመተባበር በሃዋሳ ከተማ ባለፈው ሳምንት ያከሄደው ታላቅ ህዝባዊ ጉባኤ ልካሄድ የነበረው መጋቢት 2/2007 ኣ / ም ቢሆንም፤ የሲዳማ ዞን እና የሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር ኣዳራሽ በመከልከላቸው የተነሳ ወደ መጋቢት 20 2006 ኣ / ም ለማስተላለፍ መገደዱ ታውቋል። ጉባኤውን ለማካሄድ እንደኣማራጭ ተይዞ ከነበሩት መሰብሰቢያ ኣዳራሾች መካከል የሲዳማ ባህል ኣዳራሽ ኣንዱ ሲሆን፤ ባህል ኣዳራሹን የሚያስተዳድረው የሲዳማ ዞን ኣዳራሹ በተመሳሳይ ቀን በሌላ ሰብሰባ መያዙን የምገልጽ ምላሽ ሰጥቷል። በሁለተኛ ኣማራጭነት የተያዘው በሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር ውስጥ የምገኙ ኣደራሾች ሲሆን፤ የከተማዋ ኣስተዳደር የመሰብሰቢያ ኣዳራሽ እንድፈቅድ በደብዳቤ ተጠይቆ ዛሬ ነገ በማለት ምላሽ ሳይሰጥ ቆይቶ በኃላ ላይ ኣዳራሽ እንደሌለው በመግለጽ ምላሽ መስጠቱ ታውቋል። በህዝብ ገንዘብ ለህዝብ ግልጋሎት እንድሰጥጡ የተገነቡትን እንዚህ ኣዳራሽ ለመጠቀም የተደረገው ጥረት በገዥው ፓርቲ ኣስተዳደሮች በመከልከሉ ሲኣን / መድረክ ፊታቸውን ወደ ግል ኣዳራሾች በማዞር በሃዋሳ በሴንቴራል ሆቴል ኣዳራሽ የተከራዩ ቢሆንም፤ የሆቴሉ ባለቤት በገዥው ፓርቲ ኣባላት ማስፈራሪ እንደደረሳቸው በመግለጽ ለኣዳራሽ መከራያ የተሰጣቸውን ገንዝብ መልሰዋል። የሆነ ሆኖ ለጉባኤው ሶስት ቀ