Posts

ይታሰብበት!

Image
ከዘረፋ ያልዳነው ሀዋሳ ከተማና እና እድለኛ ያልሆነው የሲዳማ ቡና ክለብ ከማህበራዊ መረብ ከ ላይ የተገኘ በ Hagerselam Haroressa ስለሀዋሳ ስነሳ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ውበት ብቻ አይደለም የሚነሳው፡፡ ተፈጥሮ የለገሰቻትን ውበት ምክንያት በማድረግ በህጋዊ መንገድ ወደ ከተማይቱ ከምተመው ኢትዮጵያዊ ህዝብ በላቄ መልኩ በህገ ወጥ መንገድ ሾልኮ በመግባት ከተማይቱንና የአካባቢውን ህብረተሰብ እረፍት የሚነሳ ከጊዜ ወደ ጊዜ መጠኑ እያሻቀበ መተዋል፡፡ ለዚህ የመንግሥት አካላት በተለይም የከተማው ማዘጋጃ ጽ/ቤት እና ከንቲባው ጽ/ቤት ይህ ነው የሚባል የማስተካከል እርምጃ ስወስዱ አይታዩም፡፡ ይልቁንም ከሌቦች ጋር በመተባበር የከተማውን ወረራ ያፋጥናሉ እንጂ፡፡  አሁን ደግሞ በያዝነው ሳምንት ተመሳሳይ የዘረፋ ተግባር በሀዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤትና እሱን ከላይ ሆኖ ከሚቆጣጠሩት እራሳቸውን መርጦ ባለሥልጣን የሆኑ አካላት የ ከተማይቱን የዘረፋ ሂደት እየተፋፋሜ ነው የሚል ነገር በስፋት ይነገራል፡፡ የከተማሞችን ”አዲሱ ሊዝ አዋጅ” ህብረተሰቡን ለወጉ እንኳን ሳያወያይ በፍጥነት ተግባራዊ በማድረግ የንግድና የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ የማግኘት እድል መካከለኛ ገቢ ላለው ማኅበረሰብ ክፍል በተለይም ለጭቁኑ መንግስት ሰራተኛ ዝግ በማድረግ እየተሻረከና እየነገደ ያለው የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ለ34 ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ተጫዋቾች በሀዋሳ ከተማ ውስጥ ቦታ ጀባ ማለቱ ተሰምተዋል፡፡  ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ደረጃ ለሚገኙ ሲዳማ ቡና እግር ኳስ ተጫዋቾች መኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ እንዲሰጣቸው ተወስኖ የነበረ ቢሆንም የከተማ አስተዳደር ፍቃደኛ ሳይሆን መቅረቱ ይታወሳል፡፡ የሀዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ብሩ ወልደ ለ

ኢትዮጵያና ኬንያን ከሚያገናኘው የሐዋሳ ሞያሌ መንገድ የተወሰነው ተጠናቀቀ

Image
አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 25፣ 2006  (ኤፍ.ቢ.ሲ ) ኢትዮጵያና ኬንያን ሚያገናኘው የሐዋሳ ሞያሌ የመንገድ ፕሮጀክት የተወሰነው በመጠናቀቀቅ ላይ ነው። በአጠቃላይ የአዋሳ ሞያሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በ5 ነጥብ 3 ቢሊዮን የሚገነባ ሲሆን ፥ ስድስት ተቋራጮችም እየተሳተፉበት ይገኛል ። የሀዋሳ-ሞያሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ኢትዮጵያን ከጎረቤት ሀገራት ጋር በየብስ ለማገናኘት እየተገነቡ ካሉ የመንገድ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው። ለአብነትም ለመንገዱ አምስተኛ ክፍል የሆነው የያቤሎ ሜጋ ፕሮጀክት ግንባታ የተጠናቀቀ ሲሆን ፥ ከሃገረ ማሪያም እስከ ያቤሎ ያለው የመንገዱ አራተኛ ክፍልም በቀጣይ ዓመት ይጠናቀቃል ተብሎ ነው የሚጠበቀው። ሌሎቹ የመንገዱ ክፍሎች በዚህ ዓመት ግንባታቸው የተጀመሩ ሲሆን ፥ በቀጣዩ ዓመት የሚጀመሩም እንዳሉ ነው በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ወንድሙ የሚናገሩት ። የፕሮጀክቶቹ የጊዜ መራራቅ የተከሰተው በተቋራጮች በቶሎ ወደ ስራ አለመግባት መሆኑን የሚናገሩት አቶ ሳምሶን ፥ 186 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የሀዋሳ-ሀገረ ማርያም መንገድም ለሶስት ተቋራጮች ተከፍሎ በዚህ ዓመት ግንባታው መጀመሩን ገልፀዋል ። ኢትዮጵያን ከኬንያ ጋር የሚያገናኘውና  በሶስት አመታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው የመንገዱ የመጨረሻ ክፍልም በዚህ አመት መጨረሻ ላይ ግንባታው የሚጀመር ሲሆን ፥ ሙሉ መንገዱ ተጠናቆ ወደ ስራ ሲገባም የሁለቱን ሀገራት የንግድ ትስስር ይበልጥ  እንደሚያጠናክረው ሃላፊው ገልፀዋል ። ኢትዮጵያም ለኬንያ ከምትልካቸው ምርቶቿ የምታገኘው ገቢ ዝቅተኛ የሚባል የነበረና በአንፃሩ ኬንያ በምስራቅ አፍሪካ ካላት ኢንቨስትመንት በኢትዮጵያ ያለው አናሳ መሆኑ ነው የሚነገ

Poverty Is a Moral Problem

Image
Development economist William Easterly says too much aid undermines the rights of the poor. William Easterly, professor of economics at New York University, is one of the most prominent iconoclasts in the field of international aid. In 2006 he published  White Man's Burden: Why the West's Efforts to Aid the Rest Have Done So Much Ill and So Little Good.  Kent Annan ( Following Jesus Through the Eye of the Needle; After Shock ) talked with him on a frigid Manhattan day over hot green tea the day after the launch of his new book,  The Tyranny of Experts: Economists, Dictators, and the Forgotten Rights of the Poor  (2014) . What are the "forgotten rights of the poor"? The rights of the poor should be the same as the rights of the rich: the core, inalienable rights that started with the language of the Declaration of Independence, including the idea that governments exist by the consent of the governed. There is an ongoing debate around the world between the a

ኣድማጭ ያጣ የሲዳማ ህዝብ የመልካም ኣስተዳደር እጦት እሮሮ

Image
ተጻፈ በሀገሬሰላም ሆሮረሳ  ምንጭ፦ የሲዳማ ኣርነት ግንባር( ሲነግ) ድህረ_ገጽ ፤ http://sidamaliberation-front.org/  የዓለም ህዘብ በስሱና የኢትዮጵያ ህዝብ በጥልቀት እንደሚያውቀው የሲዳማ ህዝብ በደል፣ህገመንግሥታዊ መብት መጣስና ድፍጠጣ፣ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መካድና የሲዳማ ህዝብ ሀብት መበዝበዝ ረዥም ዘመናትን ያስቆጠረ መሆኑን በቅን ልቦና ለሚመለከት ለማንኛውም ሰው ግልጽ ነው፡፡የሲዳማ ህዝብም በሚፈጸምበት ግፍ መማረሩንና ሥራዓቱን ሊታገሠው አለመቻሉን ግልጽ በመድረግ ለነጻነቱ እየታገለ ይገኛል፡፡  ወቅቱን እየጠበቁ በሚፈራረቁ ካድሮች የሚሰቃየው የሲዳማ ህዝብ አሁን ደግሞ ኑሮ ውድነቱና ብልሹ አስተዳደር የህዝቡን አንድነት  እያናጉ ይገኛሉ፡፡   የኢህአዴግ ተላላኪዎች በሚያቀርቡት ‘በሬ ወለደ ፕሮፓጋንዳ’ የሲዳማ ህዝብ የመለያየት እርኩስ መንፈስ የተጠናወተውን ነገር ግን  የማይበቅለውን ዘር እየዘሩም ይገኛሉ፡፡ እንደዚህ እንዲል ያነሳሳኝ ካለፈው ሁለት ዓመታት ጀምሮ ይበልጥ እየተጠናከረ የመጣውን  የሲዳማ ህዝብ ትግል ያስፈራው ኢህአዴግ/ሕወኻት መንግስት በአቶ አድሱ ለገሰ በኩል የሲዳማ ክልል ለመጎብኘት ብቅ ብሎ ከክልሉ የተለያዩ ዞኖችንና ወረዳዎንች በመሄድ የነበረውን(ያለውን) የፖለትካ ውጥረት ለመቃኘትም ጭምር አብዛኞቻችን እናውቃለን፡፡ በዚህ ጉዞው የተለያዩ የሲዳማ ህብረተሰብ ክፍል ያነጋገሩ ሲሆን የጋጠማቸውም የሥርዓቱ ባዶነትን ቁልጭ አድርጎ እንዳሳየው ህደቱን በቅርበት ስከታተል ከነበረው ምንጫችን ለማወቅ ተችለዋል፡፡  ነገር ግን የተሰማውን የሲዳማ ህዝብ ዘርፈ ብዙ ችግሮች(multidimensional problems) ወደ ጎን ትተው ‘’የሲዳማ ህዝብ በራሱ  ብሔርና ብሔረሰብ ስብስ

የቀጣዩ ዓመት 5ኛው ምርጫ ህጋዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፖለቲካ ፓርቲዎች የበኩላችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል አሉ

Image
አዲስ አበባ መጋቢት 24/2006 አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች በቀጣዩ ዓመት የሚካሄደው 5ኛው አገር አቀፍ ምርጫ ህጋዊ፤ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ  የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ። ኢዜአ ካነጋገራቸው  ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች መካከል ሰማያዊ ፓርቲ፣ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ)የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ(ኢዴፓ) ይገኙበታል። የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ፓርቲው በምርጫው የህዝቡን ይሁንታ ለማግኘት ግልጽ ፖሊሲና ስትራቴጂ  በመከተል ሰላማዊ ትግሉን መቀላቀሉን ገልጸዋል።   የምርጫ ዝግጅት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን የሚጠይቅና የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ለውጥ ለማረጋገጥ ዋነኛ መሳሪያ በመሆኑ ፓርቲው አባላትን በማፍራትና እጩዎች በመመልመል ላይ ይገኛል። ምርጫው ፍትሃዊና ህጋዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅም ፓርቲው የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ሊቀመንበሩ ተናግረዋል።                      የቅንጅት ለአንድነትና ዲሞክራሲ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሳሳሁልህ ከበደ በበኩላቸው የፓርቲው አባላት የድርጅቱን ህግንና ደንብ መሰረት በማድረግ ምርጫው ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊነት የበኩላቸውን እንዲወጡ ያደርጋል። በቀጣዩ አመት በሚካሄደው ምርጫ ፓርቲው ብቁና ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ ለመቅረብ ከወዲሁ በአባላት ምልምላና የስነ-ምግባር ደንብ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እንደሚጀመር ገልጸዋል። አቶ ሳሳሁልህ እንዳሉት አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎችና አለም አቀፍ ድርጅቶች በአገሪቱ የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧል በሚል የሚያነሱትን ስሞታ ድርጅታቸው አይቀበለውም። በአገራና ወቅታዊ አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ  በፓርቲዎች