Posts

Fichchee- The New Year of Sidama- The Sidama people celebrate the festival en mass in their sacred place called Gudumale which is located on the beautiful city of Hawassa

Image
http://commons.wikimedia.org/wiki/File:Fichchee-_The_New_Year_of_Sidama-_The_Sidama_people_celebrate_the_festival_en_mass_in_their_sacred_place_called_Gudumale_which_is_located_on_the_beautiful_city_of_Hawassa-_2013-12-18_17-37.jpg

ሆሬ _የሲዳማ ብሄረሰብ ልጃገረዶች የዘፈን ውዝዋዜ በጋዜጠኛ ቦጋሌ ጥላሁን

Image
በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ዉስጥ ከሚገኙ አስራ ሶስት ዞኖች መካከል እጅግ በርካታ የሆነ የህዝብ ቁጥር ያለዉ የሲዳማ ዞን ነዉ። በያዝነዉ አመት በተደረገ የጥናት መረጃ የሲዳማ ዞን 3.2 ሚሊዮን ህዝብ መያዙ ተነግሮአል። የለቱ የባህል ጥንቅራችን የሲዳማ ብሄረሰብ ባህላዊ ገጽታዎችን ይቃኛል። በደቡብ ኢትዮጽያ በይርጋለም ከተማ ነዋሪ የሆነዉ ጋዜጠኛ ቦጋለ ጥላሁን የረጅም ግዜ አድማጫችን ብቻ ሳይሆን ተሳታፊም ነዉ። በኢትዮጽያ የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦችን አቅፎ በሚገኘዉ በደቡብ ዞን አጓጓጊ የሆኑ የተፈጥሮ መስቦችን አሉት የሚለን ጋዜጠኛ ቦጋለ ከአዲስ አበባ 320 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘዉ በይርጋለም ከተማ ነዋሪ ሲሆን ስለ ሲዳማ ብሄረሰብ ባህል በተለይም ሆሪ ተብሎ ስለሚታወቀዉ ያላገቡ የሲዳማ ልጃገረዶች የዘፈን ዉዝዋዜ፤ ስለ ቋንቋዉ፣ ስለ ሰርግ፣ እንዲሁም ሌሎች የባህል ገጽታዎች ያጫዉተናል። በሌላ በኩል በሲዳማ ዞን ባህልና እስፖርት ማዕከል ድምጻዊ የሆነችዉ ትብለጽ ተከስተ በሲዳማ ቋንቋ በምታዜመዉ ዘመናዊ ሙዚቃዋ በአካባቢዉ ተወዳጅነትን ማትረፍዋ ነገርላታል። የሲዳማ ዞን የተፈጥሮ መስቦች ያሉበት በቱሪስቶች የሚወደድ ድንቅ የተፈጥሮ ጸጋ ያለዉም አካባቢ ነዉ መረሃ ግብሩን ያድምጡ የሲዳማ ዞን የተፈጥሮ መስቦች

የፕሬዚዳንቱን ይቅርታ የማድረግ ሥልጣን የሚቀንስ አዋጅ ቀረበ

ሪፖርተር ጋዜጣ 12 March 2014 -   መጋቢት 3, 2006 ዓ.ም. - የፓርላማ አባላት ከሕገ መንግሥቱ ጋር እንዲጣጣም ጠይቀዋል የአገሪቱ ፕሬዚዳንትን ለሕግ ታራሚዎች ይቅርታ የማድረግ ሥልጣን የሚቀንስ አዲስ ‹‹የይቅርታ አሰጣጥና አፈጻጸም ሥነ ሥርዓት›› ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማው ቀረበ፡፡ አንዳንድ የፓርላማው አባላት ረቂቅ አዋጁ ከሕገ መንግሥቱ ጋር ይቃረናል በማለት እንዲስተካከል ጠይቀዋል፡፡ የፕሬዚዳንቱን ሥልጣንና ተግባር የሚዘረዝረው የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 71 (7) ‹‹ፕሬዚዳንቱ በሕግ መሠረት ይቅርታ ያደርጋል›› በማለት ይደነግጋል፡፡ በ1996 ዓ.ም. የወጣው በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ የሚገኘው የይቅርታ ሥነ ሥርዓት አዋጅም በሕገ መንግሥቱ ለፕሬዚዳንቱ የተሰጠውን ይቅርታ የማድረግ ሥልጣን ያጠናክረዋል፡፡ በዚህ አዋጅ መሠረት ፕሬዚዳንቱ የይቅርታ ቦርድ የውሳኔ ሐሳብን መሠረት በማድረግ፣ እንዲሁም በውሳኔ ሐሳቡ ላይ የቀረቡ መረጃዎችን ፕሬዚዳንቱ በራሱ መመዘን ለሕግ ታራሚዎች ይቅርታ እንዲያደርግ ወይም እንዲከለክል ሥልጣን ይሰጠዋል፡፡ የፕሬዚዳንቱን ይቅርታ ያገኘ ታራሚ በሕጉ መሠረት የተጣለበትን ጥሶ የተገኘ ከሆነ በይቅርታ ቦርዱ የውሳኔ ሐሳብ አቅራቢነት ፕሬዚዳንቱ የሰጠውን ይቅርታ የማንሳት መብት በዚሁ በሥራ ላይ ባለው አዋጅ ለፕሬዚዳንቱ ተሰጥቷል፡፡  ባለፈው ማክሰኞ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ግን፣ ‹‹ፕሬዚዳንቱ የይቅርታ ቦርድን የውሳኔ ሐሳብ መሠረት በማድረግ ይቅርታ ይሰጣል፤›› ሲል በረቂቁ ክፍል ሁለት አንቀጽ 4 (1) ላይ አስቀምጧል፡፡ በማከልም ቦርዱ ለፕሬዚዳንቱ የሚልከው የውሳኔ ሐሳብ ይቅርታ የተወሰነላቸውን ታራሚዎች በመተለከተ ብቻ ነው፡፡  በቦርዱ ውሳኔ አቅራቢነት

ሳቅ እንደ አማራጭ ሕክምና?

ኮከቤ የማነ የፊኛ ካንሰር እንዳለበት ያወቀው ከአሥር ዓመታት በፊት ነበር፡፡ ህመሙን ካወቀ በኋላ ከሌሎች የካንሰር ሕመምተኞች ሰምቶ ሕመሜን ቢያስታግስልኝ በማለት ወደ ሳቅ ትምህርት ቤት ይቀላቀላል፡፡ በወቅቱ ሞትን እስከመመኘት ድረስ በበሽታ ይሰቃይ እንደነበር ይናገራል፡፡ ኮከቤ የኬሞቴራፒ ሕክምና ይፈጥርበት የነበረውን ሕመም ለመቋቋምና ስቃዩን ለማስታገስ ከረዱት ዋነኛው ሳቅ እንደሆነ ይገልጻል፡፡   የካንሰር ሕክምናን አብረውት ይከታተሉ ከነበሩት መካከል ብዙዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ ተመልክቷል፡፡ በአካል የሚያውቃቸው ሲያልፉ ከማየቱም በላይ ሕይወቱ አደጋ ላይ በወደቀበት ወቅት ራሱን መሳቅ አስተምሯል፡፡ ኮከቤ ወደኋላ በትዝታ እየቆዘመ ‹‹ዕድለኛ ነኝ›› ይላል፡፡  ዛሬ የ45 ዓመት ጐልማሳ ነው፤ ባለትዳርና የልጆች አባትም ነው፡፡ በቤተ መንግሥት ውስጥ የሜዳ ቴኒስ አጫዋች የሆነው ኮከቤ ‹‹የእኔ ደስተኛ መሆን ለቤተሰቦቼም ተርፏል፤ ማታ ቤት እስክገባ ይቸኩላሉ፡፡ ምንም ችግር ቢኖር በሳቅ እናሳልፈዋለን፤›› ይላል፡፡ ደስተኛ መሆኑን የሚገልጸው ኮከቤ ልጆቹ እሱን በማየት ሲስቁ ማየት ያስደስተዋል፡፡  በዓለም የድንቅ ነገሮች መዝገብ ላይ ለሦስት ሰዓት ከስድስት ደቂቃ ያለማቋረጥ በመሳቅ ሪከርድ የጨበጠና ‹‹የዓለም የሳቅ ንጉሥ›› የሚል መጠሪያ ያገኘው በላቸው ግርማ፣ ኮከቤን ለመሰሉና ሌሎች የሳቅ ትምህርት ቤት ካቋቋመ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ በእነዚህ ዓመታት ወደ ትምህርት በመሔድ ስለ ሳቅ፣ አሳሳቅንና በሌሎች ተያያዥ ትምህርቶች ለአንድ ወር ሠልጥነው የወጡ ተማሪዎች አሉ፡፡ በአፍሪካ ባሉ አገሮች ጅማሮዎች ቢኖሩም በኢትዮጵያ የሚገኘው ትምህርት ቤት የቆየና ግንባር ቀደም እንደሆነ የተለያዩ ዘገባዎች ያመለክታሉ፡፡  በላቸው ስለሳቅ ትምህርት ቤት ሲና

Ethiopia: Ribbon Cutting Brings Addis Abeba-Nairobi Highway a Step Closer

The 100km long Yabelo-Mega road - part of the 1,000km Mombasa-Nairobi-Addis Abeba Road Corridor - will be opened for traffic on Sunday, March 9, 2014 in the presence of Worqineh Gebeyehu, minister of Transport. The inauguration, which will take place in Yabelo town - 564km from Addis Abeba in Borena Zone of the Oromia Region - will also be attended by officials from the Ethiopian Roads Authority (ERA). The African Development Bank (AfDB) has extended a 770 billion Br loan to Ethiopia for the construction of the Yabelo-Mega section of the project. The Mombasa-Nairobi-Addis Abeba Road Corridor is an important part of the Trans-African Highway, from Cairo to Cape Town. In Kenya and Ethiopia, the road is a link from Addis Ababa to Nairobi. The Kenyan section of the road between Isiolo and Moyale is about 525km and was constructed as a gravel road in 1974. On the Ethiopian Side of the border, the road is entirely bitumen-paved from Moyale to Addis Abeba. However, the section of th