Posts

ጥቂቶች ሊመነደጉ፤ ብዙዎች አሽቆልቁለዋል

ከአዲሱ ጠ/ሚኒስትር አዲስ ራዕይ እንፈልጋለን “የራበው ሥራ ፈልጐ ማግኘት የማይችልና ልጆቹን ለማስተማር አቅም ያጣ ሰው ከባርነት ነፃ ነው ማለት አይቻልም፡፡” የሚለው የአሜሪካዊው ፕሬዚዳንት ሊንደን ቢ. ጆንሰን ንግግር እውነትነት አሁን አሁን በጆሮዬ መደወሉ ራሴን እያስገረመኝ መጥቷል፡፡ የዛሬ አምስትና ስድስት ዓመት ገደማ ደራሲና ጋዜጠኛ አለማየሁ ገላጋይ፤ ስለኑሮ ውድነት ሲጽፍ ብዙዎቻችን እያነበብን ፈገግ ከማለት በቀር ብዙ ልባችን አልተነካም ነበር፡፡ ምናልባትም በጣም አልፎ አልፎ ከምናነባቸው መጣጥፎች ይልቅ መንግስት ስለ ልማት የሚነፋው ጥሩንባ አደናቁሮን ይሆናል፡፡ አሁን አሁን የመንግሥት መዝገበ ቃላት “ልማት” የሚለው ትርጓሜ ግራ እያጋባን መጥቶ ጭራሽ ወደ ብስጭት የተመነዘረብን ብዙ ነን ብዬ አስባለሁ፡፡ መንግስት ልማት የሚለው ከእኛ አፍ “ቫት” እያለ የሚነጥቃትን ገንዘብ ሰብስቦ ለሌቦች ካጠገበ በኋላ፣ በፍርፋሪዋ የሚሠራትን መንገድና ጤና ጣቢያ ወይም ትምህርት ቤት ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ “ኮንደሚኒየም” እየተባሉ የተሠሩት ቤቶች አካባቢ ያለውን ግድየለሽነት ተመልከቱ፡፡ የውሃ መፍሰሻ ቦዮቹ ገና ተሠርተው ሳያልቁ ይፈርሣሉ። ሕንፃው ውስጥ ያሉትን የግብር ይውጣ ሥራዎች ተውአቸው፡፡ ለመሆኑ ልማትና ዕድገት ምንድነው? ወረቀት ላይ የሃሰት ሪፖርቶችን ከምሮ መቀለድ ነው። ቀልድና ውሸትስ እስከ የት ያዘልቀናል? ከወር ወደ ወር ሰዎች በልተው የማደር አቅማቸውን እያጡ፣ ልጆቻቸውን ማስተማር ተራራ መቧጠጥ እየሆነባቸው ሲመጣ --- እንዴት ስለ ዕድገት ይወራል? ጋዜጠኛ መሳይ ካድሬዎች ስለልማትና እድገት ብዙ ቢለፈልፉም ከሕዝቡ የበለጠ ጓዳውን የሚያውቅ ማንም ሊኖር አይችልም፡፡ አለ ቢባልም ከተራ ቀልድነት አያልፍም፡፡ እርግጥ ነው፤ ባለፉት ሃያ ዓመታት ጥቂት

ህገመንግስትን የሚቃረን አንቀጽ ከፀረሙስና አዋጅ እንዲሰረዝ ተወሰነ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በፓርላማ የወጣውን ህግ ሲያሻሽል አሁን የመጀመሪይው ነው፡፡ የቀድሞ መከላከያ ሚኒስትር አቶ ስዬ አብርሃ ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርበው ውድቅ ተደርጐባቸው ነበር፡፡  “በሚኒስትር ማዕረግ የገቢዎችና ጉምሩክ ባስልጣን ዋና ዳሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ ላይ የቀረበው የሙስና ክስ መታየት ያለበት በከፍተኛ ፍ/ቤት ነው ወይስ በጠቅላይ ፍ/ቤትን” በሚል ለተነሳው ጉዳይ ምላሽ ለመስጠት ለሰዓታት የተከራከሩ የፌደሬሽን ምክር ቤት አባላት፤ የሚኒስትሮች ክስ በጠቅላይ ፍ/ቤት እንዲታይ የሚደነግገው አንቀጽ ከፀረ ሙስና አዋጁ እንዲሰረዝ በ76 የድጋፍና በ8 የተቃውሞ ድምጽ ወሰኑ፡፡  የሙስና ክሶችን በቀዳሚነት የመዳኘት ስልጣን የከፍተኛ ፍ/ቤት እንደሆነ የሚገልፀው የፀረሙስና አዋጅ፣ ሚኒስትሮች ሊከሰሱ ግን በቀጥታ ወደ ጠቅላይ ፍ/ቤት እንደሚቀርብ ይገልፃል፡፡ በ1993 ዓ.ም ኢህአዴግ ውስጥ በተከሰተው ፀብ ከፓርቲው አመራርነት የተባረሩት የቀድሞ መከላከያ ሚኒስትር ስዬ አብርሃ፣ በወቅቱ በሙስና መከሰሳቸው የሚታወቅ ሊሆን፣  ጉዳያቸው በቀጥታ በጠቅላይ ፍ/ቤት እንዲታይ መደረጉን ተቃውመው እንደነበር ይታወሳል፡፡ እንደሌሎች ተከሳሾች የአቶ ስዬ ክስ በከፍተኛ ፍ/ቤት እንዲታይ መከራከሪያ ያቀረቡት ጠበቃ፤ አለበለዚያ ግን ይግባኝ የመጠየቅ የተከሳሽ ህገመንግስታዊ መብትን የሚጥስ ይሆናል ብለዋል፡፡  በፀረ ሙስና አዋጅ የተካተተው አንቀጽ ህገመንግስቱን ስለሚቃረን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ቀርቦ ውሳኔ እንዲሰጥበት የአቶ ስዬ ጠበቃ ቢከራከሩም፤ ፍ/ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል፡፡  ጥያቄው እንደገና ፍ/ቤት ውስጥ የተነሳው ከአስር አመታት በኋላ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ከፍተኛ ሃላፊዎች ላይ ከተመሰረተው ክስ ጋር ተያይዞ ነው፡፡ በአንድ በኩል ዋና ዳሬክተሩ አቶ መላ

የሐዋሳ ሐይቅን «ደህንነት ለመጠበቅ ተኝተን አናድርም» - የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ዮናስ ዮሴፍ

Image
የሐዋሳ ሐይቅን ከብክነት ለመከላከል የከተማው ነዋሪም ሆነ በአካባቢ ጥበቃ ላይ የተሠማሩ አካላት ሚናቸውን ማጐልበት ይጠበቅባቸዋል፤ ለመጥለቅ የዳዳችው ጀምበር ሙሉ ለሙሉ ከእይታ ከመሰወሯ በፊት ከአድማሱ ጥግ ሆና የፈነጠቀችው ነፀብራቅ የሐይቁን ውበት አጉልቶታል። አእዋፍ ከእንቅስቃሴያቸው እየተገቱ በሐይቁ አካባቢ በሚገኙ ትልልቅ ዛፎች ላይ መቀመጥ ጀምረዋል፤ ድምፃቸውም ብዙም አይሰማም። በነፋሱ ኃይል በሚገፋው የሐይቁ ውሃ ላይ ሆነው ጥቂት አዕዋፋት ወዲያ ወዲህ ይላሉ። በሐይቁ እምብርት ላይ በርቀት ሲታዩ የነበሩት ጀልባዎችም ወደ ሐይቁ ዳር እየተፋጠኑ ናቸው። ወጣቶች፣ ጎልማሶችና አዛውንቶች በሐይቁ ዙሪያ ታድመዋል። የዲላ ከተማ ነዋሪው አቶ ሳሙኤል ንጉሴ በንግድ ሥራቸው ምክንያት ወደ ሃዋሳ ከተማ ይመላለሳሉ። ቢያንስ በወር አንዴ ብቅ እንደሚሉም ነው የሚናገሩት። « ፍቅር የሆነውን የሃዋሳ ሐይቅ ሳልጎበኝ በጭራሽ አልመለስም » ይላሉ። ወሩን ሙሉ በሥራቸው ምክንያት የተፈጠረባቸውን ጫና በሐይቁ በሚያደርጉት የደቂቃዎች ቆይታ እርግፍ አድርገው አስወግደው በአዲስ መንፈስ እንደሚመለሱም ነው የሚናገሩት። ወይዘሮ ማርታ አክሊሉም ልክ እንደ አቶ ሳሙኤል ወደ ሐይቁ ሲመጡ እፎይታ ይሰማቸዋል። « በሐይቁ ዳር ዳር ሆቴሎች መኖራቸው መልካም ነው » የሚሉት አስተያየት ሰጪዋ፤ አልፎ አልፎ የሚያስደምጡት ሙዚቃ በሐይቁ ዳርቻ ላይ እፎይ ብሎ መቀመጥ የሚፈልግን ሰው ምቾት እንደሚነሳነው የገለጹት። « በሐይቁ ዙሪያ ያለው ተፈጥሮአዊ ትዕይነት ብቻ በራሱ በቂ ነው » ባይ ናቸው። ለከተማዋ ውበት አስተዋጽኦ ካደረጉት መካከል የመጀመሪያውን ስፍራ የሚይዘው የሐዋሳ ሐይቅ ደህንነቱን ለመጠበቅ « ተኝተን አናድርም » ይላሉ የከተማው ከንቲባ አቶ ዮ

በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተነሳው ቃጠሎ በሰው ሕይወት ላይ ጉዳት አላደረሰም

Image
በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በመገንባት ላይ ባለው ህንፃ ላይ ከትናንት በስቲያ ምሽት የእሳት አደጋ ቃጠሎ ተነስቶ በአካባቢው ህብረተሰብና በተለያዩ አካላት በተደረገው ርብርብ በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ፡፡ የዩኒቨርሲቲው የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ መልሰው ደጀኔ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ ከትናንት በስቲያ ከምሽቱ አራት ሰዓት ገደማ በሴት ተማሪዎች ማደሪያ አካባቢ እየተገነባ ባለ አንድ ህንፃ ላይ ባልታወቀ መንስኤ የእሳት አደጋ ቃጠሎ ተነስቶ ከሁለት ሰዓታት በላይ በፈጀ ርብርብ በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል፡፡ የአካባቢው ህብረተሰብ ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር አፋጣኝ እርምጃ በመውሰዱ ቃጠሎው የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ማድረግ ተችሏል። ዩኒቨርሲቲው ከክልሉ ፖሊስ ጋር በመሆን ተማሪዎቹን የማረጋጋት ሥራ መሥራቱን አስታውቀዋል፡፡ የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀልና የትራፊክ አደጋ መከላከል ዋና የሥራ ሂደት ባለቤት ኮማንደር በላይነህ በቀለ በበኩላቸው፤ እሳቱን ለማጥፋት የተለያዩ አካላት ተሳትፎ ያደረጉ መሆኑን ጠቅሰው፣ በዋናነትም ከአካባቢው ህብረተሰብ፣ ከተማሪዎች፣ ከሃዋሳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ፣ ከፖሊስ ኮሚሽንና ከሻሸመኔ እሳት አደጋ መከላከል እንዲሁም በአካባቢው መንገድ ሥራ ላይ ከተሰማሩ አካላት ድጋፍ የተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የእሳት ቃጠሎ አደጋውን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከሁለት ሰዓታት በላይ መፍጀቱን ኮማንደር በላይነህ ተናግረው፣ ይህም ሊሆን የቻለው ቃጠሎው የተከሰተበት ህንፃ በግንባታ ላይ ስለሚገኝና እሳቱን በፍጥነት በቁጥጥር ስር ለማዋል አስቸጋሪ ስላደረገው በመሆኑ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡ በተጠንቀቅ ላይ የነበ

የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ መልካም ተሞክሮዎችና ያልተሻገራቸው መሥመሮች

Image
በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በመማር ማስተማር፣ በምርምር ሥራዎች፣ በማሕበረሰብ አገልግሎትና የሰባ ሰላሳ ቅበላን ተግባራዊ ለማድረግ የመምህራንና ቤተ ሙከራ ቁሶችን ከማሟላት አንጻር ያጋጠሙ ችግሮች እንዲሁም በተወሰዱ መፍትሔዎችና በሌሎችም ጉዳዮች ከፕሬዚዳንቱ ዶክተር ዮሴፍ ማሞ ጋር ያደረግነውን ቃለ ምልልስ በክፍል አንድ ይዘን መቅረባችን ይታወሳል። በዛሬው እትማችን በዩኒቨርሲቲው ሌሎች እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ያደረግነውን ቆይታ ይዘን ቀርበናል። አዲስ ዘመን ፦ በዩኒቨርሲቲው ወጣቶችን በተለይም ሴቶችን ከትምህርታቸው የሚያሰናክሉ የተለያዩ ችግሮች እንደሚያጋጥሙ ይነገራል። ይህ ምን ያህል እውነት ነው ? ምን የመፍትሔ እርምጃስ ተወሰደ ? ዶክተር ዮሴፍ፦ የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በርካታ ተማሪዎችን ያቀፈ ነው። ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል እጅግ በጣም ጥቂት በሚባሉ ተማሪዎች የተነሳ የአብዛኛው ስም መነሳት የለበትም። ተቋሙ እነዚህም ቢሆኑ ለተለያዩ ችግሮች መጋለጥ የለባቸውም የሚል አቋም ይዞ እየሰራ ነው። ያለው አመለካከት በጣም የተዛባ ነው። አብዛኛዎቹ ሴት ተማሪዎችም ቢሆኑ እኛ ለመማር ነው የመጣነው፤ አላማ አለን የሚሉ ናቸው። ከዚህ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ሴት ተማሪዎችን ሰብስበን ለማወያየት ስንፈልግ አይመጡም። ምክንያታቸው በተወሰኑ ተማሪዎች የተነሳ ሰብዕናችንን ትነካላችሁ የሚል ነው። ሐዋሳ ትልቅ ከተማ በመሆኑ በወሲብ ሥራ ላይ የተሰማሩ ሴቶች ሳይቀሩ ራሳቸውን ተማሪ በማስመሰል « ሹገር ዳዲ » የሚባሉትን ያጠምዳሉ። የተማሪ መታወቂያ ይዘውም ይገኛሉ። ይህን ችግር ለመፍታት ከከተማው ፖሊስ ጋር በመተባበር እየሰራን ነው። በመምህራን በኩልም ከውጤት ጋር በተያያዘ ከሴት ተማሪዎች ጋር አግባብ ያልሆነ ግንኙነት ለመፍጠር የሞከረ አንድ መምህር እንዲ