Posts

ህገመንግስትን የሚቃረን አንቀጽ ከፀረሙስና አዋጅ እንዲሰረዝ ተወሰነ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በፓርላማ የወጣውን ህግ ሲያሻሽል አሁን የመጀመሪይው ነው፡፡ የቀድሞ መከላከያ ሚኒስትር አቶ ስዬ አብርሃ ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርበው ውድቅ ተደርጐባቸው ነበር፡፡  “በሚኒስትር ማዕረግ የገቢዎችና ጉምሩክ ባስልጣን ዋና ዳሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ ላይ የቀረበው የሙስና ክስ መታየት ያለበት በከፍተኛ ፍ/ቤት ነው ወይስ በጠቅላይ ፍ/ቤትን” በሚል ለተነሳው ጉዳይ ምላሽ ለመስጠት ለሰዓታት የተከራከሩ የፌደሬሽን ምክር ቤት አባላት፤ የሚኒስትሮች ክስ በጠቅላይ ፍ/ቤት እንዲታይ የሚደነግገው አንቀጽ ከፀረ ሙስና አዋጁ እንዲሰረዝ በ76 የድጋፍና በ8 የተቃውሞ ድምጽ ወሰኑ፡፡  የሙስና ክሶችን በቀዳሚነት የመዳኘት ስልጣን የከፍተኛ ፍ/ቤት እንደሆነ የሚገልፀው የፀረሙስና አዋጅ፣ ሚኒስትሮች ሊከሰሱ ግን በቀጥታ ወደ ጠቅላይ ፍ/ቤት እንደሚቀርብ ይገልፃል፡፡ በ1993 ዓ.ም ኢህአዴግ ውስጥ በተከሰተው ፀብ ከፓርቲው አመራርነት የተባረሩት የቀድሞ መከላከያ ሚኒስትር ስዬ አብርሃ፣ በወቅቱ በሙስና መከሰሳቸው የሚታወቅ ሊሆን፣  ጉዳያቸው በቀጥታ በጠቅላይ ፍ/ቤት እንዲታይ መደረጉን ተቃውመው እንደነበር ይታወሳል፡፡ እንደሌሎች ተከሳሾች የአቶ ስዬ ክስ በከፍተኛ ፍ/ቤት እንዲታይ መከራከሪያ ያቀረቡት ጠበቃ፤ አለበለዚያ ግን ይግባኝ የመጠየቅ የተከሳሽ ህገመንግስታዊ መብትን የሚጥስ ይሆናል ብለዋል፡፡  በፀረ ሙስና አዋጅ የተካተተው አንቀጽ ህገመንግስቱን ስለሚቃረን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ቀርቦ ውሳኔ እንዲሰጥበት የአቶ ስዬ ጠበቃ ቢከራከሩም፤ ፍ/ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል፡፡  ጥያቄው እንደገና ፍ/ቤት ውስጥ የተነሳው ከአስር አመታት በኋላ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ከፍተኛ ሃላፊዎች ላይ ከተመሰረተው ክስ ጋር ተያይዞ ነው፡፡ በአንድ በኩል ዋና ዳሬክተሩ አቶ መላ

የሐዋሳ ሐይቅን «ደህንነት ለመጠበቅ ተኝተን አናድርም» - የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ዮናስ ዮሴፍ

Image
የሐዋሳ ሐይቅን ከብክነት ለመከላከል የከተማው ነዋሪም ሆነ በአካባቢ ጥበቃ ላይ የተሠማሩ አካላት ሚናቸውን ማጐልበት ይጠበቅባቸዋል፤ ለመጥለቅ የዳዳችው ጀምበር ሙሉ ለሙሉ ከእይታ ከመሰወሯ በፊት ከአድማሱ ጥግ ሆና የፈነጠቀችው ነፀብራቅ የሐይቁን ውበት አጉልቶታል። አእዋፍ ከእንቅስቃሴያቸው እየተገቱ በሐይቁ አካባቢ በሚገኙ ትልልቅ ዛፎች ላይ መቀመጥ ጀምረዋል፤ ድምፃቸውም ብዙም አይሰማም። በነፋሱ ኃይል በሚገፋው የሐይቁ ውሃ ላይ ሆነው ጥቂት አዕዋፋት ወዲያ ወዲህ ይላሉ። በሐይቁ እምብርት ላይ በርቀት ሲታዩ የነበሩት ጀልባዎችም ወደ ሐይቁ ዳር እየተፋጠኑ ናቸው። ወጣቶች፣ ጎልማሶችና አዛውንቶች በሐይቁ ዙሪያ ታድመዋል። የዲላ ከተማ ነዋሪው አቶ ሳሙኤል ንጉሴ በንግድ ሥራቸው ምክንያት ወደ ሃዋሳ ከተማ ይመላለሳሉ። ቢያንስ በወር አንዴ ብቅ እንደሚሉም ነው የሚናገሩት። « ፍቅር የሆነውን የሃዋሳ ሐይቅ ሳልጎበኝ በጭራሽ አልመለስም » ይላሉ። ወሩን ሙሉ በሥራቸው ምክንያት የተፈጠረባቸውን ጫና በሐይቁ በሚያደርጉት የደቂቃዎች ቆይታ እርግፍ አድርገው አስወግደው በአዲስ መንፈስ እንደሚመለሱም ነው የሚናገሩት። ወይዘሮ ማርታ አክሊሉም ልክ እንደ አቶ ሳሙኤል ወደ ሐይቁ ሲመጡ እፎይታ ይሰማቸዋል። « በሐይቁ ዳር ዳር ሆቴሎች መኖራቸው መልካም ነው » የሚሉት አስተያየት ሰጪዋ፤ አልፎ አልፎ የሚያስደምጡት ሙዚቃ በሐይቁ ዳርቻ ላይ እፎይ ብሎ መቀመጥ የሚፈልግን ሰው ምቾት እንደሚነሳነው የገለጹት። « በሐይቁ ዙሪያ ያለው ተፈጥሮአዊ ትዕይነት ብቻ በራሱ በቂ ነው » ባይ ናቸው። ለከተማዋ ውበት አስተዋጽኦ ካደረጉት መካከል የመጀመሪያውን ስፍራ የሚይዘው የሐዋሳ ሐይቅ ደህንነቱን ለመጠበቅ « ተኝተን አናድርም » ይላሉ የከተማው ከንቲባ አቶ ዮ

በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተነሳው ቃጠሎ በሰው ሕይወት ላይ ጉዳት አላደረሰም

Image
በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በመገንባት ላይ ባለው ህንፃ ላይ ከትናንት በስቲያ ምሽት የእሳት አደጋ ቃጠሎ ተነስቶ በአካባቢው ህብረተሰብና በተለያዩ አካላት በተደረገው ርብርብ በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ፡፡ የዩኒቨርሲቲው የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ መልሰው ደጀኔ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ ከትናንት በስቲያ ከምሽቱ አራት ሰዓት ገደማ በሴት ተማሪዎች ማደሪያ አካባቢ እየተገነባ ባለ አንድ ህንፃ ላይ ባልታወቀ መንስኤ የእሳት አደጋ ቃጠሎ ተነስቶ ከሁለት ሰዓታት በላይ በፈጀ ርብርብ በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል፡፡ የአካባቢው ህብረተሰብ ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር አፋጣኝ እርምጃ በመውሰዱ ቃጠሎው የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ማድረግ ተችሏል። ዩኒቨርሲቲው ከክልሉ ፖሊስ ጋር በመሆን ተማሪዎቹን የማረጋጋት ሥራ መሥራቱን አስታውቀዋል፡፡ የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀልና የትራፊክ አደጋ መከላከል ዋና የሥራ ሂደት ባለቤት ኮማንደር በላይነህ በቀለ በበኩላቸው፤ እሳቱን ለማጥፋት የተለያዩ አካላት ተሳትፎ ያደረጉ መሆኑን ጠቅሰው፣ በዋናነትም ከአካባቢው ህብረተሰብ፣ ከተማሪዎች፣ ከሃዋሳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ፣ ከፖሊስ ኮሚሽንና ከሻሸመኔ እሳት አደጋ መከላከል እንዲሁም በአካባቢው መንገድ ሥራ ላይ ከተሰማሩ አካላት ድጋፍ የተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የእሳት ቃጠሎ አደጋውን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከሁለት ሰዓታት በላይ መፍጀቱን ኮማንደር በላይነህ ተናግረው፣ ይህም ሊሆን የቻለው ቃጠሎው የተከሰተበት ህንፃ በግንባታ ላይ ስለሚገኝና እሳቱን በፍጥነት በቁጥጥር ስር ለማዋል አስቸጋሪ ስላደረገው በመሆኑ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡ በተጠንቀቅ ላይ የነበ

የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ መልካም ተሞክሮዎችና ያልተሻገራቸው መሥመሮች

Image
በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በመማር ማስተማር፣ በምርምር ሥራዎች፣ በማሕበረሰብ አገልግሎትና የሰባ ሰላሳ ቅበላን ተግባራዊ ለማድረግ የመምህራንና ቤተ ሙከራ ቁሶችን ከማሟላት አንጻር ያጋጠሙ ችግሮች እንዲሁም በተወሰዱ መፍትሔዎችና በሌሎችም ጉዳዮች ከፕሬዚዳንቱ ዶክተር ዮሴፍ ማሞ ጋር ያደረግነውን ቃለ ምልልስ በክፍል አንድ ይዘን መቅረባችን ይታወሳል። በዛሬው እትማችን በዩኒቨርሲቲው ሌሎች እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ያደረግነውን ቆይታ ይዘን ቀርበናል። አዲስ ዘመን ፦ በዩኒቨርሲቲው ወጣቶችን በተለይም ሴቶችን ከትምህርታቸው የሚያሰናክሉ የተለያዩ ችግሮች እንደሚያጋጥሙ ይነገራል። ይህ ምን ያህል እውነት ነው ? ምን የመፍትሔ እርምጃስ ተወሰደ ? ዶክተር ዮሴፍ፦ የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በርካታ ተማሪዎችን ያቀፈ ነው። ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል እጅግ በጣም ጥቂት በሚባሉ ተማሪዎች የተነሳ የአብዛኛው ስም መነሳት የለበትም። ተቋሙ እነዚህም ቢሆኑ ለተለያዩ ችግሮች መጋለጥ የለባቸውም የሚል አቋም ይዞ እየሰራ ነው። ያለው አመለካከት በጣም የተዛባ ነው። አብዛኛዎቹ ሴት ተማሪዎችም ቢሆኑ እኛ ለመማር ነው የመጣነው፤ አላማ አለን የሚሉ ናቸው። ከዚህ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ሴት ተማሪዎችን ሰብስበን ለማወያየት ስንፈልግ አይመጡም። ምክንያታቸው በተወሰኑ ተማሪዎች የተነሳ ሰብዕናችንን ትነካላችሁ የሚል ነው። ሐዋሳ ትልቅ ከተማ በመሆኑ በወሲብ ሥራ ላይ የተሰማሩ ሴቶች ሳይቀሩ ራሳቸውን ተማሪ በማስመሰል « ሹገር ዳዲ » የሚባሉትን ያጠምዳሉ። የተማሪ መታወቂያ ይዘውም ይገኛሉ። ይህን ችግር ለመፍታት ከከተማው ፖሊስ ጋር በመተባበር እየሰራን ነው። በመምህራን በኩልም ከውጤት ጋር በተያያዘ ከሴት ተማሪዎች ጋር አግባብ ያልሆነ ግንኙነት ለመፍጠር የሞከረ አንድ መምህር እንዲ

Ethiopian coffee industry recieves a boost for 2014

Image
Ethiopia is the birthplace of Coffea arabica, the ‘mountain coffee’, and is some of the best tasting commercially produced type of coffee in the world. Now, people associated with the coffee trade in the African nation will be celebrating the start of this year in style after humanitarian groups combined in order to bring funding for a new facility near the central-southern town of Yirgachefe (also transliterated as Irgachefe), securing around two-hundred jobs in the process. Ethiopian coffee group  METAD  will run the site after securing the investment from a project initiated by the East Coast Impact Angel Network (EIAN), and facilitated by the U.S Agency for International Development’s (USAID) Agricultural Growth Program which aims to secure and develop industrial growth in hard-to-reach areas where food and medical supplies are limited. Out of the jobs created, seventy percent will go to women whilst the benefits of this project will spread to around four-hundred local co