የከተማ መሬት ምዝገባ አዋጅን ለማፅደቅ የተቸገረው ፓርላማ የፌዴሬሽን ምክር ቤትን ይሁንታ ጠየቀ...የኣዋጁ መጽደቅ የሃዋሳን ከተማ የወደ ፊት እጣ ፋንታ ይወስነዋል
የከተማ መሬት ምዝገባ አዋጅን ለማፅደቅ የተቸገረው ፓርላማ የፌዴሬሽን ምክር ቤትን ይሁንታ ጠየቀ...ፓርላማው ይህንን ሕግ በማውጣት የክልል ከተሞችን መሬት መመዝገብና ማስተዳደር ለፌዴራል መንግሥት ሊሰጥ ይችላል ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 51(5) እና 52(2) (መ) መሠረት ለፌዴራሉ መንግሥት መሬትና የተፈጥሮ ሀብቶችን የሚመለከቱ ሕጎችን የማውጣት ሥልጣን የሚሰጥ ሲሆን፣ ክልሎች ደግሞ በፌዴራሉ መንግሥት የሚወጡ ሕጎችን መሠረት በማድረግ መሬት የማስተዳደር ሥልጣን እንዳላቸው የሚደነግግ በመሆኑ፣ ፓርላማው ይህንን ሕግ በማውጣት የክልል ከተሞችን መሬት መመዝገብና ማስተዳደር ለፌዴራል መንግሥት ሊሰጥ ይችላል የሚለው አስቸጋሪ ጉዳይ እንደሆነበት አስረድቷል፡፡ ኣዋጁ ከጸደቀ በፌዴራል መንግስት ልተዳደሩ ከምችሉ የክልል ከተሞች መካከል ሃዋሳ ከተማ ይገኝበታል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር የቀረበለትን የከተማ መሬትና መሬት ነክ ንብረቶች ምዝገባ ረቂቅ አዋጅ በስፋት ሲመረምር ቢቆይም፣ አዋጁን ለማፅደቅ ፓርላማው ሕገ መንግሥታዊ ሥልጣን አለው ወይ የሚለው አጠያያቂ በመሆኑ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ ይሁንታ እንዲሰጠው ጠየቀ፡፡ ረቂቅ አዋጁ ‹‹የከተማ መሬት ምዝገባ አዋጅ›› የሚል ስያሜ የተሰጠው ቢሆንም፣ የአዋጁ አጠቃላይ ይዘት ግን ዜጎች በመሬት ላይ ለሚገነቡት ቋሚ ንብረት የባለቤትነትና የመጠቀም መብት ዕውቅናና ዋስትና መስጠትን የሚመለከት ነው፡፡ ረቂቅ አዋጁ የከተማ መሬትን በተመለከተ ‹‹በማንኛውም ክልል የከተማ አስተዳደር ወሰን ውስጥ የሚገኝ መሬት ነው›› የሚል ትርጓሜ የሚሰጥ ሲሆን፣ የአዋጁ ተፈጻሚነት ወሰንን በተመለከተ ደግሞ፣ ‹‹ይህ አዋጅ የከተማ መሬትን በሚመለከት በአገሪቱ ውስጥ