‹‹በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከሥራ ይልቅ ለወሬና ለአሉባልታ ጊዜያቸው የሚያጠፉ አሉ››
አቶ ዱቤ ጅሎ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ዳይሬክተር አገሪቱ በአትሌቲክሱ የምትሳተፍባቸው በርካታ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ውድድሮች ከፊት ለፊቷ ይጠብቃታል፡፡ ወቅቱ ደግሞ የውድድር ዓመቱ የመጀመሪያው ሩብ በጀት ዓመት ተጠናቆ ቀጣዩ የተጀመረበት ነው፡፡ ስፖርቱን በበላይነት የሚመራው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ግን ዝምታን መርጧል፡፡ በሌላ በኩል በአንድም ሆነ በሌላ የሚመለከታቸው አካላት የብሔራዊ ፌዴሬሽኑን ዝምታ እንዳልወደዱት የሚናገሩ አሉ፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ ተቋሙ ባለፈው መስከረም 22 እና 23 ቀን 2006 ዓ.ም. 17ኛውን መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤው ድሬዳዋ ላይ ባከናወነበት ወቅት፣ አገሪቱ እስከዛሬ ከተለመዱት የውድድር ዓይነቶች በተጨማሪ አዳዲስ የሜዳ ተግባራትን ጨምሮ በአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ ለመሳተፍ ዕቅድ እንዳላት፣ ለዚያ ደግሞ ከሙያተኞች ምርጫ እስከ አትሌቶች ምልመላ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ ስምምነት ላይ መድረሱ ነው፡፡ የአገሪቱ የስፖርት መገናኛ ብዙሃኑ እግር ኳሱ ላይ በተለይ ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአፍሪካ ዋንጫ እስከ ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የተጓዘበትን መንገድ ብቻ ትኩረት ማድረጉ አትሌቲክሱን ጨምሮ የተቀረው እንዲዘነጋ ሆኗል ይላሉ፡፡ ይህም ለስፖርቱ ዘርፍ አደገኛ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ እነዚህንና ሌሎች ጥያቄዎችን በመያዝ ደረጀ ጠገናው በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ዳይሬክተር ከሆኑት አቶ ዱቤ ጁሎ ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡ • የውድድር ዓመቱ ሩብ ዓመት ተገባዷል፡፡ ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ እርስዎ ከሚመሩት የቴክኒክ ክፍል ጭምር ዝምታን መርጧል የሚሉ ቅሬታዎች ይቀርባሉ፡፡ መግለፅ የምችለው ቴክኒኩን በተመለከተ ነው፡፡ እንደሚታወቀው ባለፈው ዓመት በርካታ