የባንኮች የውጭ ምንዛሪ ግዢና አጠቃቀም ግልጽነት ይጐድለዋል
የኢትዮጵያ ንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ከሚያገኝባቸው ምንጮች መካከል የውጭ ንግድ (Export) እና በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በባንኮች በኩል የሚልኩት ገንዘብ (Remittance) ዋናዎቹ ናቸው፡፡ መንግሥት የውጭ ንግዳችን እንዲያድግና ለገቢ ንግዳችን (Import) የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት ሰፊ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በዋናነት በቡና ላይ ተመሥርቶ የነበረው የውጭ ንግዳችን ዛሬ መሠረቱ ሰፍቶ አበባ፣ ቆዳ፣ ጨርቃ ጨርቅ፣ የቅባት እህሎች፣ የቁም ከብቶችና ሌሎችም ተጨምረዋል፡፡ በውጭ ንግድ ላይ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች መሬት በአነስተኛ ዋጋ ከማቅረብ ጀምሮ ከውጭ የሚያስገቧቸው መሠረታዊ ዕቃዎች በአብዛኛው ከቀረጥና ታክስ ነፃ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ላኪዎች ገንዘብ ከባንኮች በአነስተኛ ወለድ ያገኛሉ፡፡ ከባንኮች ለሚበደሩት ገንዘብም መንግሥት ዋስትና የሚሰጥበት አግባብ አለ፡፡ ምርታቸውንም ተወዳዳሪ እንዲሆን ያለምንም ቀረጥና ታክስ ወደ ውጭ አገር ልከው እንዲሸጡ ይፈቀድላቸዋል፡፡ ታዲያ ይህ ሁሉ ማበረታቻ ተደርጎለት የሚገኝ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀም ላይ ክፍተት ይታያል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ አገር ገንዘቦች መግዣና መሸጫ ዋጋን ይወስናል፡፡ የየቀኑ የውጭ ምንዛሪ መግዣና መሸጫም ዋጋም በሬድዮና በቴሌቪዥን ከምንስማው ባፈነገጠ መልኩ ባንኮች ከመግዣ ዋጋ በተጨማሪ በመግዣና በመሸጫ መካከል ባለው ዋጋ (Mid rate)፣ አንዳንዴም በመሸጫ ዋጋ (Selling rate) ከላኪዎች (Exporters) እንደሚገዙ ይሰማል፡፡ በተለይ የዚህ ዓይነት የውጭ ምንዛሪ ግዢ በአገሪቱ የጠረፍ ከተሞች በኩል ከሚወጡ ዕቃዎች ሽያጭ በሚገኝ የውጭ ምንዛሪ ላይ እንደሚበረታታ ውስጥ አዋቂዎች ይገልጻሉ፡፡ አፈጻጸሙም ግልጽነት የጎደለው፣ ሙስ