Posts

ለአክሲዮን ማህበራት የትርፍ ክፍፍል ግብር አዲስ መመሪያ ተግባራዊ ሆነ

Image
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 13 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ)  የአክሲዮን ማህበራት የትርፍ ክፍፍል ግብርን አስመልክቶ አዲስ የአፈፃፃም መመሪያ ተግባራዊ ሆነ። አዲሱ መመሪያ የትርፍ ክፍፍል ሳይደረግ በአክሲዮን ባለድርሻዎች ለተጨማሪ ኢንቨስትመንት እንዲውል በቃለ ጉባኤ ከተወሰነ እና ይህንንም በህጋዊ መንገድ ማረጋገጥ ከተቻለ ከትርፍ ክፍፍል ታክስ ነፃ ያደርጋቸዋል መመሪያው ። በመመሪያው መሰረት በሰነዶች ማረጋጋጫና በንግድ ሚኒስቴር ሳይረጋገጥ ለተጨማሪ ኢንቨስትመንት ውሏል የሚል ምክንያት ቦታ የሌለው ሲሆን ፥ የትርፍ ክፍፍሉም እንደተፈፀመ ታሳቢ ተደርጎ 10 በመቶ የትርፍ ክፍፍል ታክስ እንዲከፍሉ ይደረጋል ነው ያለው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን። ከሀምሌ 30 ጀምሮ ተግባራዊ በሆነው በዚህ መመሪያ ዙሪያ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ዛሬ ተወያይቷል። የቀደሞው ንግድ ህግ ክፍተቶች በ19 94 ዓ.ም የወጣው የንግድ ህግ ላይ ማንኛውም የአክሲዮን እና ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በየዓመቱ ከሚያገኘው ትርፍ እና ለአባላቱ ከሚያከፋፍለው ትርፍ ውስጥ 10 በመቶ ግብር እንዲከፍል ይደነግጋል። ይህን ህግ በፍጥነት ተግባራዊ በማድረጉ በኩል በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን    የትርፍ ክፍፍል ግብሩንም እያሳወቀ በመክፈል ረገድ በንግዱ ማህበረሰብ በኩል በነበረው ክፍተት በሚገባ ተግባራዊ ሳይሆን ቆይቷል ። ህጉ የኩባንያዎቹ ትርፍ ለአባላት ሲከፋፈል ግብር እንደሚከፈል ይገልፃል ። አብዛኛዎቹ የንግዱ ማህበረሰብ አባለት ደግሞ ይህን ትርፍ ለአባላቶቻችን እስካላከፋፈልን ድረስ የ10 በመቶ ግብርን መክፈል እንደማይገደዱ በመግለፅ ለካፒታል ማስፋፊያ አውለነዋል የሚል ምክንያት የሚያቀርቡበት ሁኔታ ነበር ። የለም ኩባንያዎቹ አመ

ፊቼ እና ጫምባላላ - የሲዳማ ዓመት ዋዜማና መባቻ

Image
የአንድ ማኅበረሰብ መገለጫና መለያ ከሆኑት እሴቶች አንዱና ዋነኛው ባህል እንደሆነ የመስኩ ምሁራን ይገልጻሉ፡፡ የአንድ ማኅበረሰብ የኑሮ ዘይቤ የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መርሕ እምነትና አስተሳሰብ የጥበብ፣ የአስተዳደር፣ የአለባበስና አመጋገብ ሥርዓት፣ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎችና መገልገያዎች የባህል መገለጫዎች ሲሆኑ በዋናነት በሁለት የሚከፈሉት ቁሳዊና መንፈሳዊ ተብለው ነው፡፡ ቁሳዊ ባህል ታሪካዊ ቅርሶች በጽሑፍ የተቀመጡ ሕትመቶችና ሰነዶች ሕንፃዎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች የምርትና አገልግሎት መሳሪያዎችንና ሌሎች ተያያዥ ውጤቶችን ያጠቃልላል፡፡ መንፈሳዊ ባህል በሌላ በኩል የሃይማት ( እምነት ) ፣ ፍልስፍና፣ ርዕዮተ ዓለም፣ የፖለቲካ አስተሳሰብ፣ ማኅበራዊ ክንዋኔዎች ( ክብረ በዓላት ) እና አመለካከቶችን ያካትታል፡፡   የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ ፈቼና አዲሱ ዓመት ክብረ በዓል መንፈሳዊ ( ኢንታንጀብል ) ባህል ከሆኑት አንዱ ሲሆን፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሻገር የመጣ የብሔሩ ማንነት መገለጫ እንደሆኑ የሲዳማ ዞን ባህል ቱሪዝምና መንግሥት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ዓመታዊ መጽሔት ያሰፈረው መረጃ ያመለክታል፡፡ ሲዳማ የራሱ የሆኑ የቀን አቆጣጠር ያለው ሲሆን የአሮጌው ዓመት ማለቂያ እና የአዲሱ ዓመት መጀመሪያ   ትክክለኛ ዕለት የብሔሩ   ሊቃውንት ( አያንቶ ) ተወስኖ ይታወጃል፡፡ የፊቼ ጫምባላላ በዓል በዓለም መንፈሳዊ ቅርስነት ለማስመዝገብ እንቅስቃሴ የተጀመረ ሲሆን ቅድመ ምዝገባ የመጀመሪያ ዙር መረጃ የማሰበሰ