Posts

ፊቼ እና ጫምባላላ - የሲዳማ ዓመት ዋዜማና መባቻ

Image
የአንድ ማኅበረሰብ መገለጫና መለያ ከሆኑት እሴቶች አንዱና ዋነኛው ባህል እንደሆነ የመስኩ ምሁራን ይገልጻሉ፡፡ የአንድ ማኅበረሰብ የኑሮ ዘይቤ የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መርሕ እምነትና አስተሳሰብ የጥበብ፣ የአስተዳደር፣ የአለባበስና አመጋገብ ሥርዓት፣ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎችና መገልገያዎች የባህል መገለጫዎች ሲሆኑ በዋናነት በሁለት የሚከፈሉት ቁሳዊና መንፈሳዊ ተብለው ነው፡፡ ቁሳዊ ባህል ታሪካዊ ቅርሶች በጽሑፍ የተቀመጡ ሕትመቶችና ሰነዶች ሕንፃዎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች የምርትና አገልግሎት መሳሪያዎችንና ሌሎች ተያያዥ ውጤቶችን ያጠቃልላል፡፡ መንፈሳዊ ባህል በሌላ በኩል የሃይማት ( እምነት ) ፣ ፍልስፍና፣ ርዕዮተ ዓለም፣ የፖለቲካ አስተሳሰብ፣ ማኅበራዊ ክንዋኔዎች ( ክብረ በዓላት ) እና አመለካከቶችን ያካትታል፡፡   የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ ፈቼና አዲሱ ዓመት ክብረ በዓል መንፈሳዊ ( ኢንታንጀብል ) ባህል ከሆኑት አንዱ ሲሆን፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሻገር የመጣ የብሔሩ ማንነት መገለጫ እንደሆኑ የሲዳማ ዞን ባህል ቱሪዝምና መንግሥት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ዓመታዊ መጽሔት ያሰፈረው መረጃ ያመለክታል፡፡ ሲዳማ የራሱ የሆኑ የቀን አቆጣጠር ያለው ሲሆን የአሮጌው ዓመት ማለቂያ እና የአዲሱ ዓመት መጀመሪያ   ትክክለኛ ዕለት የብሔሩ   ሊቃውንት ( አያንቶ ) ተወስኖ ይታወጃል፡፡ የፊቼ ጫምባላላ በዓል በዓለም መንፈሳዊ ቅርስነት ለማስመዝገብ እንቅስቃሴ የተጀመረ ሲሆን ቅድመ ምዝገባ የመጀመሪያ ዙር መረጃ የማሰበሰ

የፍትሕ ስባቷና ተደራሽነቷ

የፍትሕ ተደራሽነትን (Access to justice) የፅንሰ ሐሳብ ትንተናና በአገራችን ያለውን አተገባበር መፈተሽ ለባለድርሻ አካላት (ለሕዝቡ፣ ለመንግሥት የፍትሕ አካላት እንዲሁም በመብት ላይ ለሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች) ያለው አስተዋጽኦ ሰፊ ነው፡፡ የፍትሕ ተደራሽነት የፍትሕ ፅንሰ ሐሳብ አካል ተደርጎ የሚወስድ ሲሆን፣ በራሱም የግለሰቦች መብት ነው፡፡ የፍትሕ ተደራሽነት ባልተረጋገጠበት ሁኔታ ባለመብት መሆን ትርጉም ያጣል፡፡ በሕግ የተቀመጡ መብትና ግዴታን አለማወቅ (ወይም ለማወቅ የሚያስችል ሁኔታ አለመኖር)፣ ቢታወቅም የሕግ ባለሙያ ዕርዳታ ባለማግኘት ወይም የዳኝነት ሥልጣን ያላቸው አካላት ተደራሽነት ባለመረጋገጡ መብትን አለመጠየቅ ወይም ለተጣሰ መብት ሕጋዊ መፍትሔ አለማግኘት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው፡፡ ለመሆኑ በአገራችን ያሉ ሕጐች ለግለሰቦች የፍትሕ ተደራሽነት መብት ዋስትና ይሰጣሉ? የመብቱ አፈጻጸምስ በተግባር ምን ይመስላል? የሚሉትን ነጥቦች በፌዴራል ደረጃ መዳሰስ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ነው፡፡ የፍትሕ ተደራሽነት መብት ትርጉም በፅንሰ ሐሳብ ደረጃ የፍትሕ ተደራሽነት መብት የፍትሕ ፈላጊውን ማዕከል በማድረግ ሰፋ ያለ ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ የፍትሕ ተደራሽነት አንድን አጋጣሚ ብቻ የሚመለከት ሳይሆን፣ ፍትሕ ፈላጊው መብቱን ለማስከበር ተገቢ የሆነ መፍትሔ ለማግኘት የሚከተለውን ሒደት በሙሉ ያጠቃልላል፡፡ ግለሰቦች በተለይ ለመብት ጥሰት የተጋለጡ ሰዎች የደረሰባቸውን ኢፍትሐዊነት ለማወቅ የሚያስችላቸውና ኢፍትሐዊነቱ የሕግ የበላይነትን ወይም ሕግን መሠረት አድርጐ እንዲታረም በመንግሥት ተቋማት ውስጥ መፍትሔ የሚያገኙበትን ሒደት የፍትሕ ተደራሽነት መብት ልንለው እንችላለን፡፡ የፍትሕ ተደራሽነት በውስጡ ብዙ መብቶችን የሚያካትት ቢሆንም፣ በዚህ ጽ

የፍትሕ ስባቷና ተደራሽነቷ

የፍትሕ ተደራሽነትን (Access to justice) የፅንሰ ሐሳብ ትንተናና በአገራችን ያለውን አተገባበር መፈተሽ ለባለድርሻ አካላት (ለሕዝቡ፣ ለመንግሥት የፍትሕ አካላት እንዲሁም በመብት ላይ ለሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች) ያለው አስተዋጽኦ ሰፊ ነው፡፡ የፍትሕ ተደራሽነት የፍትሕ ፅንሰ ሐሳብ አካል ተደርጎ የሚወስድ ሲሆን፣ በራሱም የግለሰቦች መብት ነው፡፡ የፍትሕ ተደራሽነት ባልተረጋገጠበት ሁኔታ ባለመብት መሆን ትርጉም ያጣል፡፡ በሕግ የተቀመጡ መብትና ግዴታን አለማወቅ (ወይም ለማወቅ የሚያስችል ሁኔታ አለመኖር)፣ ቢታወቅም የሕግ ባለሙያ ዕርዳታ ባለማግኘት ወይም የዳኝነት ሥልጣን ያላቸው አካላት ተደራሽነት ባለመረጋገጡ መብትን አለመጠየቅ ወይም ለተጣሰ መብት ሕጋዊ መፍትሔ አለማግኘት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው፡፡ ለመሆኑ በአገራችን ያሉ ሕጐች ለግለሰቦች የፍትሕ ተደራሽነት መብት ዋስትና ይሰጣሉ? የመብቱ አፈጻጸምስ በተግባር ምን ይመስላል? የሚሉትን ነጥቦች በፌዴራል ደረጃ መዳሰስ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ነው፡፡ የፍትሕ ተደራሽነት መብት ትርጉም በፅንሰ ሐሳብ ደረጃ የፍትሕ ተደራሽነት መብት የፍትሕ ፈላጊውን ማዕከል በማድረግ ሰፋ ያለ ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ የፍትሕ ተደራሽነት አንድን አጋጣሚ ብቻ የሚመለከት ሳይሆን፣ ፍትሕ ፈላጊው መብቱን ለማስከበር ተገቢ የሆነ መፍትሔ ለማግኘት የሚከተለውን ሒደት በሙሉ ያጠቃልላል፡፡ ግለሰቦች በተለይ ለመብት ጥሰት የተጋለጡ ሰዎች የደረሰባቸውን ኢፍትሐዊነት ለማወቅ የሚያስችላቸውና ኢፍትሐዊነቱ የሕግ የበላይነትን ወይም ሕግን መሠረት አድርጐ እንዲታረም በመንግሥት ተቋማት ውስጥ መፍትሔ የሚያገኙበትን ሒደት የፍትሕ ተደራሽነት መብት ልንለው እንችላለን፡፡ የፍትሕ ተደራሽነት በውስጡ ብዙ መብቶችን የሚያካትት ቢሆንም፣ በዚህ ጽ

በ40/60 ምዝገባ ለመመዝገብ ለምሹ የሲዳማ ዳይስፖራ

በ40/60 ቤቶች ግንባታ ፕሮግራም ምዝገባ ሒደት በመረጃ ፍሰት መደነቃቀፍ ግራ መጋባት ውስጥ የነበሩ የዳያስፖራ አባላት በሳምንቱ መጨረሻ መረጃቸውን እያስተካከሉ ምዝገባ መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ፡ በሌላ በኩልም ባንኩ ከ500 ሺሕ እስከ 800 ሺሕ የሚደርሱ ሰዎች በዚህ የ40/60 ፕሮግራም ይመዘገባሉ ብሎ ቅድሚያ ግምት ቢሰጥም፣ ባለፈው ዓርብ ምሽት ማተሚያ ቤት እስከገባንበት ሰዓት ምዝገባ ያካሄዱ ሰዎች ቁጥር  ከታሰበው እጅግ ያነሰ (81,257) መሆኑ ታውቋል፡፡  የ40/60 ቤቶች ምዝገባ ባለፈው ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ 116 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎችና መገናኛ አካባቢ ከአምቼ ፊት ለፊት በሚገኘው የአዲስ አበባ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ተጀምሯል፡፡ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ውስጥ የሚካሄደው ምዝገባ በውጭ አገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን (ዳያስፖራ) የተመደበ ነው፡፡ በዚህ የምዝገባ ጣቢያ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በግንባር ቀርበው ወይም በወኪላቸው አማካይነት ምዝገባ ያካሂዳሉ፡፡ ነገር ግን በተለይ በውጭ አገር ሆነው በግንባር መቅረብ ያልቻሉ ኢትዮጵያውያን ከሌላ ምንጭ የሚሰሙት መረጃና ከወኪላቸው የሚሰሙት መረጃ እየተጣረሰባቸው ግራ ተጋብተው መሰንበታቸውን የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡ ምዝገባው በተጀመረባቸው የመጀመሪያዎቹ ቀናት የምዝገባ ፍሰቱ መደነቃቀፉንና በሳምንቱ መጨረሻ ፍሰቱ እየተስተካከለ መምጣቱን፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ባንኩ በዳያስፖራዎች ምዝገባ ጣቢያ ገለጻ በመስጠት ያለውን የመረጃ ክፍተት በመሙላት ላይ ሲሆን፣ እስከ ዓርብ ምሽት ድረስ በአጠቃላይ ከተመዘገቡት ውስጥ ሦስት

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ብቃት ያለው የሰው ኃይል በማፍራት ኢንዱስተሪዎችን ሊደግፉ ይገባል-ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም

Image
አዲስ አበባ ነሐሴ 11/2005 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ብቃት ያለው የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ ኢንዱስትሪዎችን መደገፍ እንደሚገባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ አሳሰቡ። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን ለ20 ቀናት ሲወስዱ የቆየውን የአቅም ግንባታ ሥልጠና ዛሬ በይፋ ተጠናቋል። የትምህርት ሚኒስቴር 1 ሺህ 700 የሚሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዝዳንቶች፣ የዩኒቨርስቲ ፋኩልቲ ዲኖችና የዲፓርትመንት ኃላፊዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር ዛሬ በአፍሪካ ኅብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሂደዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት የተጀመረውን አገራዊ ዕድገት ለማፋጠንና ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሠልጥኖ የሚወጣው የሰው ኃይል ብቃቱ የተረጋገጠ መሆን ይገባዋል። ለኢንዱስትሪ ልማት መፋጠን እያንዳንዱ ዩኒቨርስቲ በየአካባቢው ከሚገኙ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ብቃት ያላቸው ተማሪዎችን እንዲቀረፁ በማስቻል ረገድ አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚጠበቅባቸውም አመልክተዋል። አገሪቱ ከድህነት ለማውጣት በሚደረገው ጥረት ፈጣንና ሁሉን አቀፍ ተጠቃሚ የሚያረጋግጥ ቀጣይነት ያለው ሥራ ለመስራት ግብርናው ወሳኝ ሚና መጫወቱን እንደሚቀጥል ጠቁመዋል። የአገሪቱን የግብርና ዘርፍ በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን ለማስቻል እየታዩ ያሉትን ጅምር ዕድገቶች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በምርምርና ስርፀት አስደግፈው ሊሰሩ እንደሚገባቸው አቶ ኃይለማሪያም አስገንዝበዋል። በዚህ በኩል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚያደርጉትን ጥረት ለመደገፍ መንግሥት በተቻለው አቅም ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። በመላ አገሪቱ የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ምሁራንና የመስኩ ባለሙያዎች አገራ