ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለሁለት መምህራን የፕሮፌሰርነት ማእርግ ሰጠ
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 4ሺህ723 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡ ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለ14 ጊዜ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 4 ሺህ 723 ተማሪዎች በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ አስመርቋል፡፡ከተመራቂዎች ውስጥ 556ቱ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው፡፡ ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለሁለት መምህራን ንጋቱ ረጋሳ እና ተስፋየ ሲመና የፕሮፌሰርነት ማእርግ ሰጥቷል፡፡ በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ 1ሺህ 352 ተማሪዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ ሀምሌ 6/2005 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ከተመራቂዎች በመጀመሪያ ዲግሪ 489 ወንዶችና 182 ሴቶች፣ በሁለተኛ ዲግሪ 515 ወንዶችና 166 ሴቶች ናቸው፡፡ http://www.ertagov.com/amharic/index.php/component/k2/item/1342-%E1%88%83%E1%8B%8B%E1%88%B3-%E1%8B%A9%E1%8A%92%E1%89%A8%E1%88%AD%E1%88%B2%E1%89%B2-%E1%88%88%E1%88%81%E1%88%88%E1%89%B5-%E1%88%98%E1%88%9D%E1%88%85%E1%88%AB%E1%8A%95-%E1%8B%A8%E1%8D%95%E1%88%AE%E1%8D%8C%E1%88%B0%E1%88%AD%E1%8A%90%E1%89%B5-%E1%88%9B%E1%8A%A5%E1%88%AD%E1%8C%8D-%E1%88%B0%E1%8C%A0