የኢሜግሬሽንና ዜግነት ጉዳዮች ዋና መምሪያ አዋሳ በሚገኘው ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ ከህገ ወጥ ደላሎች ጋር በመመሳጠር ተገልጋዮችን አንገላተዋል ያላቸውን 11 ሰራተኞች በህግ ቁጥጥር ስር ዋሉ
አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6 ፣ 2005 (ኤፍ.ቢ. ሲ) የኢሜግሬሽንና ዜግነት ጉዳዮች ዋና መምሪያ በስራዬ ላይ እንቅፋት ሆነዋል ባላቸው የተቋሙ ሰራተኞችና ህገወጥ ደላሎች ላይ ከሚመለከታቸው አካለት ጋር በመሆን በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ አደረገ፡፡ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረጉት ተቋሙ አዋሳ በሚገኘው ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ ከህገ ወጥ ደላሎች ጋር በመመሳጠር ተገልጋዮችን አንገላተዋል ያላቸውን አስራ አንድ ሰራተኞቹ ፡፡ የኢሚግሬሽን ዜግነት ጉዳዮች ዋና መምሪያ የሚሰጠው አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ አይደለም በዚህም ለእንግልት እየተዳረግን ነው የሚሉና መሰል አቤቱታዎች በተገልጋዩ ዘንድ የሚነሱ ቅሬታዎች ናቸው፡፡ ተቋሙ የችግሩ መንስኤዎች የህግ ወጥ የደላሎች መበራከትና አሁን ካለው የኪራይ ሰብሳቢነት ችግር ተያይዞ የመጣ መሆኑን በመግለፅ ፤ ለዚህም ያካሄድኳቸው ግምገማዎችና ክትትሎች ማሳያ ናቸው ብሏል፡ የዋና መምሪው ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ሀይለ ጊዮርጊስ እንደሚሉት ፥ አዲስ አበባ በሚገኘው ዋናው ተቋም የሚስተዋለው የአገልግሎት መጨናነቅ ህገወጥ ደላሎች ለፓስፖርት ፈላጊዎች በሚሰጡት የተሳሳተ መረጃ ምክንያት የተከሰተ ነው ብለዋል፡፡ “በክልሎች ተመሳሳይ አገልግሎት የሚሰጡ ስድስት መስሪያ ቤቶች ቢኖሩም ህገወጥ ደላሎቹ ተጨማሪ ብር ለማግኘት ትክክለኛው ፓስፖርት ያለው አዲስ አበባ ነው በማለትና ተገልጋዩን ቪዛ እናመጣላችዋለን እያሉ ፓስፖርታቸውን እየቀሙ ይወስዳሉ " ብለዋል፡፡ በህገወጥ ደላሎችና በአንዳንድ የተቋሙ ሰራተኛች መካከል ተፈጥሮ የነበረው የጥቅም ትስስርም ሌላኛው የችግሩ መንስኤ መሆኑን ነው አቶ ጌታቸው ያስረዱት፡፡ ህገወጥ ደላሎቹ ከሰራተኛቹ ጋር በመመሳጠር ባለጉዳዮች ገንዘብ ከከፈሉ ፓስፖርት የሚወሰድበ