Posts

Digital Shift for Commodity Exchange

Image
The Ethiopian Commodity Exchange (ECX) is looking to expedite the process of developing technology for an online trading system, by the end of the second quarter of 2013.  After developing the technology, it is expecting to launch online trading on the exchange floor and six other remote trading sites, by the end of June 2014. The project is estimated to cost 4.1 million dollars. The 2013 deadline is part of the conditions that the Investment Climate for Africa Fund (ICF) requires the ECX to meet, in order for it to sign a revised financing agreement for the project. In a rush to meet these conditions, the ECX has started working on the technology in-house, and has extended the contract of Solomon Edossa – part of the original Ethiopian Diaspora management team that served as chief information officer for five years and had stayed back to serve as an advisor until mid 2013. Now his contract has been extended until 2014, in order for him to head the project. The ECX is also loo

አንድነት የፀረ-ሽብር አዋጁን ለማሰረዝ የ1ሚ. ሰዎችን ፊርማ ያሰባስባል

ዶ/ር ነጋሶ የመጀመሪያው ፈራሚ ሆነዋል “የአገሩን በሬ በአገሩ ሰርዶ እንጂ በውጭ ተቋማት መተማመንይቅር” - ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማሪያም አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) ከትላንት በስቲያ በይፋ የጀመረው ህዝባዊ ንቅናቄ የፀረ-ሽብር አዋጁን ማሰረዝ ዋነኛ አላማው እንደሆነ ገለፀ፡፡ ለዚህ ዓላማውም የአንድ ሚሊዮን ሰዎችን የድጋፍ ፊርማ (ፒቲሽን) በዕለቱ ማስፈረም የጀመረ ሲሆን የመጀመሪያው ፈራሚ የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ሆነዋል፡፡ ፓርቲው የፀረ-ሽብር ህጉን ለማሰረዝ ከሚንቀሳቀስባቸው ምክንያቶች አንዱ ህገ-መንግስቱን በእጅጉ የሚጥስና የኢትዮጵያን ዜጐች በማጥቃት የሚጀምር በመሆኑ ነው ብሏል - የህዝባዊ ንቅናቄው ኮሚቴ በሠጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡ ፓርቲው “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል የጀመረው የሶስት ወር ንቅናቄ የአንድ ሚሊዮን ህዝቦችን ድምፅ በማሰባሠብ የአገሪቱን ዜጐችና ተቋማትን በማጥቃት፣ በሀይማኖት ጣልቃ በመግባት፣ ከአባትና እናት የተወረሠን ንብረትና ሀብት በሽብርተኝነት ስም የሚገፈውን አዋጅ ለማሰረዝ ጥረት እናደርጋለን፤ ወደ ክስም እንሄዳለን” ብሏል፡፡ “ይህ ማለት ግን ኢትዮጵያ ካላት ተፈጥሯዊ ሀብትና መሠል ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የፀረ-ሽብር ህግ አያስፈልጋትም ማለት እንዳልሆነ የገለፁት የንቅናቄው ኮሚቴ አባል አቶ ትዕግስቱ አወል፤ አሁን ስራ ላይ ያለው የፀረ ሽብር አዋጅ ግን ሰዎችን እና ተቋማትን የሚያጠቃ ነው ብለዋል፡፡ ከተጠቁት ተቋማት ውስጥ አንድነትና መድረክ ዋነኞቹ እንደሆኑ፣ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ ሰዎችም የዚሁ አዋጅ ሠለባ መሆናቸውን፣ እንዲሁም ከህገ መንግስቱ ጋርም በከፍተኛ ሁኔታ ስለሚቃረን ትኩረት አድርገንበታል ሲሉም አክለዋል፡፡ “ምንም እንኳን በፍትህ ተቋማቱ ላይ ያለን እምነት የተሸ

የሐዋሳ ስታዲየም ግንባታ በመፋጠን ላይ ይገኛል

Image
የስታዲየሙ ግንባታ በአሁኑ ወቅት  23  በመቶ ያህል የተጠናቀቀ ሲሆን ከተያዘለት የጊዜ ገደብ አስቀድሞ እንዲጠናቀቅ ሥራው እየተፋጠነ ይገኛል፤ በቀድሞ አጠራሩ  « ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ስታዲየም »  በአሁኑ ደግሞ  « አዲስ አበባ ስቴዲየም  »  የአፍሪካ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ መዲና ለሆነችው አዲስ አበባ የአገሪቱንና የክለቦችን ዓለም አቀፍ ውድድሮች የምታስተናግድበት ብቸኛው ስፍራ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። ሠላሳ አምስት ሺ ተመልካቾችን የመያዝ አቅም እንዳለው የሚነገርለት የአዲስ አበባ ስቴዲየም በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ 1940  እንደተገነባ የተለያዩ መረጃዎች ያመለክታሉ። ስታዲየሙ በአውሮፓውያኑ  1962 ፣  1968 ና  1976  የተካሄዱ ሦስት የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታዎች ተስተናግደውበታል። ኢትዮጵያ ካስተናገደቻቸው ከእነዚህ ሦስት የአፍሪካ ዋንጫዎች መካከል ሦስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ባለድልም ሆናበታለች። አዲስ አበባ ስታዲየም የአፍሪካ የወጣቶች ሻምፒዮናና  16 ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮናም በብቃት ተስተናግደውበታል። ይህ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ እድሜ ያስቆጠረውና በመዲናዋ በብቸኝነት ደከመኝ ሰለችኝ ሳይል ከአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ውድድሮች በተጨማሪ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች የሚካሄዱበት ስታዲየም  « አንድ ለእናቱ  »  እየተባለ የሚጠራበት ጊዜ ማብቂያ የተቃረበ ይመስላል። ለዚህ ማሳያው ደግሞ በአማራ፣ በትግራይ፣ በኦሮሚያና በደቡብ ክልሎች በባሕር ዳር፣ በመቀሌ፣ በነቀምትና በሐዋሳ ከተሞች በመገንባት ላይ የሚገኙት ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች ማሳያ ሊሆኑ ይችላሉ። ከእነዚህ ስታዲየሞች መካከል ግንባታው ከተጀመረ የአንድ ዓመት እድሜ ያስቆጠረው የሐዋሳ ስታዲየም ግንባታ በመፋጠን ላይ ይገኛል። የጋዜ

የዘመን መለወጫ በሲዳማ

በሲዳማ የጊዜ አቆጣጠር መሰረት የሳምንቱ ቀናት በስም አራትናቸው። እነሱም ቃዋዶ፣ ቃዋላንካ፣ ዴላ፣ዲኮ በሚል መጠሪያ ተለይተው የታወቃሉ። እንዲሁም አንድ ወር አጋና (ጨረቃ) እና ቱንሲቾ(ጨለማ) ተብሎ በሁለት ይከፈላል። እያንዳንዱ ወር በቋንቋው ተለይቶ የሚታወቅበት የራሱ መጠሪያ (ሥያሜ) ያለው ሲሆን ፤ ወራቱ አስራ ሁለት ናቸው። በነባሩ የሲዳማ ባህላዊ የጊዜ አቆጣጠር ውስጥ ጷግሜ ፎቃ የሚል ስያሜ ተሰጥቶቷል።     በነባሩ የሲዳማ የጊዜ ቀመር አቆጣጠር መሰረት በዓመት ውስጥ ያሉት አስራ ሁለት ወራት በአራት ወቅቶች የተከፈሉ ናቸው። ከዚሁ አንጻር ወቅቶቹ አሮ(በጋ)፣ሀዋዶ(ክረምት)፣በዴሳ (በልግ) እና ቢራ (መኸር) የሚል መጠሪያ አላቸው። በባህሉና በጊዜ ቀመሩ መሰረት ሲዳማ የራሱ ዘመን መለወጫ ቀን አለው።ይህም ፍቼ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።      የዘመን መለወጫ( ፍቼ) በአል አከባበር     ፍቼ በሲዳማ ባህል በዓመት አንዴ በድምቀት የሚከበር የዘመን መለወጫ በዓል ነው። በባህሉ መሰረት አከባበሩ እስከ ሁለት ሳምንት ይዘልቃል። የፍቼ በዓል ቅደም ተከተላዊ የአከባበር ሂደቱ ከመጀመሩ በፊት ለአከባበሩ መነሻና መድረሻ የሚሆኑ ክንውኖች አሉ። ከእነዚህ ክንውኖች የመጀመሪያው ላኦ(ምልከታ) ነው። ላኦ ፍቼ መቼ እንደሚውል አያንቶዎች (የስነክዋክብት ተመልካቾች አረጋውያን) የጨረቃንና የከዋክብትን አካሄድ ጥምረት ተመልክተው የሚለዩት ሲሆን፤ አያንቶዎች ፍቼ ቀኑ መቼ እንደሚውል በከዋክብት ምልከታ ከለዩ በኋላ ለጎሳ መሪዎች ይገልጻሉ። የጎሳ መሪዎች ቀኑ ተገልጾ ለህብረተሰቡ እንዲለፈፍ ሲያዙ በገበያ ስፍራዎች በላላዋ (በልፈፋ) ይገለጻል። ላላዋ (ልፈፋ) የጎሳ መሪዎች ስር ባሉ ስፍራዎች የሚከወን ሲሆን ፤ ለፋፊዎች በገያ ቀን የበግ ቆዳ ረዠም ዘንግ ላይ ሰቅለው በመያዝ

ለእጩ ተመራቂ መምህራን የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ሊሰጥ ነው

Image
በዘንድሮው የትምህርት ዓመት ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ መምህራን የብቃት ማረጋገጫ ፈተና እንደሚሰጣቸው የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡   ሚኒስቴር ዴኤታው አቶ ፉአድ ኢብራሂም እንደተናገሩት የትምህርተ ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደርገው ጥረት የመምህራን የሞያ ብቃት ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል፡፡ ምዘናው እጩ ተመራቂዎቹ ወደ ስራ ዓለም ከመግባታቸው በፊት እንዲሰጥ መደረጉ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት የተዘረጋውን ፓኬጅ ውጤታማ በማድረግ ረገድ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል፡፡ በስራ ላይ ያሉት ነባር መምህራንም ምዘናውን እንዲወስዱ በማድረግ ወደሚፈለገው ደረጃ ለማምጣት ተከታታይ የሞያ ስልጠና ይሰጣል ማለታቸውን የዘገበው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ነው፡፡