ልብ ያልተባለው የልብ ህመም!
Written by መታሰቢያ ካሣዬ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የልብ ህመሞች በጉሮሮ ህመም ሳቢያ የሚከሰቱ ናቸው ልብ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ሥራውን ካቆመ ደም ወደ አንጐላችን መድረስ አይችልም፡፡ ይህ ደግሞ አንጐላችን ኦክስጅን እንዳያገኝ ያደርገዋል፡፡ የሰው ልጅ አንጐል ለ15 ሰኮንዶች ያህል ኦክስጅን ካላገኘ ህሊናን መሳት ይከተላል፡፡ አንጐላችን ከ10 ደቂቃ በላይ ኦክስጅን ካላገኘ ሞት ይከተላል፡፡ በዚህ መሠረታዊ የሰውነታችን አካል ላይ የሚደርስ ችግር በቀላሉ መፍትሔ ለማግኘት የሚችል ባለመሆኑ ለከፍተኛ አደጋና ሞት ያጋልጠናል፡፡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ በልብ ህመም የተያዘ ሰው የቱንም ያህል ዘመናዊ ህክምና ቢያገኝም ህመሙን ሙሉ በሙሉ ማዳንና ወደቀድሞው ሁኔታ መመለስ አይቻልም፡፡ ይህ መሠረታዊ የሆነው የአካላችን ክፍል ምንም የህመም ምልክት ሳያሳየንና ጤነኛ መስሎን በድንገት በሚፈጥረው ችግር ህይወታችን ለአደጋ ይጋለጣል፡፡ ድንገተኛ ስለሆነው የልብ ህመም መንስኤዎች፣ ምልክቶችና ህክምናዎች አስመልክቶ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶ/ር ታረቀኝ ተስፋዬ ማብራሪያ ሰጥተውናል፡፡ የልብ ህመም በአሁኑ ወቅት በአገራችን በስፋት የሚታይና ለበርካቶች ድንገተኛ ሞት መንስኤ ሆኗል። አብዛኛዎቹ የልብ ህሙማን በሽታው እንዳለባቸው እንኳን ሳያውቁ በድንገት በሚፈጠር ችግር ህይወታቸው ሲያልፍ ማየት እየተለመደ መጥቷል፡፡ ይህም ህብረተሰቡ ጤናውን ለመጠበቅና ያሉበትን የጤና ችግሮች አስቀድሞ በማወቅ ህክምናና ጥንቃቄ የማድረግ ልምድ እንደሌለው አመላካች ነው” የሚሉት ዶ/ር ታረቀኝ፤ የልብ ህመም ዓይነቶችን እንዲህ ይዘረዝሯቸዋል፡፡ ቀደም ባሉት ዘመናት የልብ ህመም የሰለጠኑት አገራት የጤና ችግር እንደሆነ ይታሰብ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ችግሩ የ