Posts

ልብ ያልተባለው የልብ ህመም!

Image
Written by  መታሰቢያ ካሣዬ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የልብ ህመሞች በጉሮሮ ህመም ሳቢያ የሚከሰቱ ናቸው ልብ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ሥራውን ካቆመ ደም ወደ አንጐላችን መድረስ አይችልም፡፡ ይህ ደግሞ አንጐላችን ኦክስጅን እንዳያገኝ ያደርገዋል፡፡ የሰው ልጅ አንጐል ለ15 ሰኮንዶች ያህል ኦክስጅን ካላገኘ ህሊናን መሳት ይከተላል፡፡ አንጐላችን ከ10 ደቂቃ በላይ ኦክስጅን ካላገኘ ሞት ይከተላል፡፡ በዚህ መሠረታዊ የሰውነታችን አካል ላይ የሚደርስ ችግር በቀላሉ መፍትሔ ለማግኘት የሚችል ባለመሆኑ ለከፍተኛ አደጋና ሞት ያጋልጠናል፡፡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ በልብ ህመም የተያዘ ሰው የቱንም ያህል ዘመናዊ ህክምና ቢያገኝም ህመሙን ሙሉ በሙሉ ማዳንና ወደቀድሞው ሁኔታ መመለስ አይቻልም፡፡ ይህ መሠረታዊ የሆነው የአካላችን ክፍል ምንም የህመም ምልክት ሳያሳየንና ጤነኛ መስሎን በድንገት በሚፈጥረው ችግር ህይወታችን ለአደጋ ይጋለጣል፡፡ ድንገተኛ ስለሆነው የልብ ህመም መንስኤዎች፣ ምልክቶችና ህክምናዎች አስመልክቶ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶ/ር ታረቀኝ ተስፋዬ ማብራሪያ ሰጥተውናል፡፡ የልብ ህመም በአሁኑ ወቅት በአገራችን በስፋት የሚታይና ለበርካቶች ድንገተኛ ሞት መንስኤ ሆኗል። አብዛኛዎቹ የልብ ህሙማን በሽታው እንዳለባቸው እንኳን ሳያውቁ በድንገት በሚፈጠር ችግር ህይወታቸው ሲያልፍ ማየት እየተለመደ መጥቷል፡፡ ይህም ህብረተሰቡ ጤናውን ለመጠበቅና ያሉበትን የጤና ችግሮች አስቀድሞ በማወቅ ህክምናና ጥንቃቄ የማድረግ ልምድ እንደሌለው አመላካች ነው” የሚሉት ዶ/ር ታረቀኝ፤ የልብ ህመም ዓይነቶችን እንዲህ ይዘረዝሯቸዋል፡፡ ቀደም ባሉት ዘመናት የልብ ህመም የሰለጠኑት አገራት የጤና ችግር እንደሆነ ይታሰብ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ችግሩ የ

የጦቢያ መንግስት ቆሞ የሚሄደው “ምቀኛ አታሳጣኝ” በሚለው ፀሎት ነው!

Written by  ኤልያስ ምቀኞች ቢበዙልን እኮ ባለ3 ዲጂት እድገት እናስመዘግብ ነበር !          አንዳንዴ የአባቶችን ተረትና ምሳሌ እንዲሁም ብሂል ዝም ብሎ ማጣጣል “ፌር” አይመስለኝም። አንዳንድ ቀለም የዘለቃቸው የጦቢያ ምሁሮችና ዘመናይ ነን ባዮች ግን እነዚህን ሥነ ቃሎች ለድህነታችንና ኋላ ቀርነታችን ሰበብ አድርገው ያቀርባሉ፡፡ አላወቁም እንጂ ጦቢያችን ከእነመንግስቷ ቆማ የምትሄደው በእነዚህ ወርቃማ አባባሎች እኮ ነው፡፡ እውነቱን ለመናገር---ከእነዚህ ምሁር ነን ባዮች እኮ የጥንቶቹ አባቶቻችን በብዙ ነገር ሺ ጊዜ ይበልጧቸዋል፡፡ እናም “ከመጠምጠም መማር ይቅደም” እላቸዋለሁ - የአባቶቻችንን ብሂሎች የሚተቹትን የጦቢያ ምሁሮች፡፡ ይሄን ግሳፄ የምሰነዝረው ግን ዝም ብዬ አይደለም፡፡ ብሂሎቹ ለጦቢያ የህልውና መሠረት መሆናቸውን ስለደረስኩበት ነው፡፡ ለዛሬ ልዩ ትኩረት አድርገን የምንፈትሸው ከጥንት የአባቶች አባባል ከወረስናቸው ሥነቃሎች መካከል “ምቀኛ አታሳጣኝ” የሚለውን ወርቃማ ብሂል ነው፡፡ እውነቴን ነው የምላችሁ --- የጦቢያችን ህልውና የተመሰረተው ሙሉ በሙሉ በእዚህ ብሂል ላይ ነው፡፡ ብታምኑኝም ባታምኑኝም “ምቀኛ አታሳጣኝ” የሚለው ሥነ ቃል ባይኖር ጦቢያችን አትኖርም ነበር፡፡ ጥናቴ እንደሚጠቁመው፤ የአበሻ ዘር ምቀኛ ያጣ ዕለት መኖር ያቆማል (አሳዛኝ ቢመስልም ሃቅ ነው!) በአጠቃላይ የዕድገታችን በሉት የስልጣኔያችን ወይም በኢህአዴግ ቋንቋ የህዳሴያችን መሰረቱ “ምቀኛ አታሳጣኝ” የሚለው መሪ ሥነ ቃል ነው፡፡ አበሻ ሲፀልይ “ምቀኛ አታሳጣኝ” ይላል ሲባል አልሰማችሁም? ቀልድ ከመሰላችሁ እንደኔ ተሸውዳችኋል፡፡ ፈፅሞ የማያጠራጥር ሃቅ መሆኑን እኔ ላረጋግጥላችሁ እችላለሁ - በመረጃም በማስረጃም፡፡ እንኳን ዜጐች ራሳቸው ፖለቲከኞችም ከዚ

በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ ከ5 ሺህ በላይ ጎልማሶች ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርት በመከታተል ላይ ናቸው ተባለ

ሃዋሳ ግንቦት 23/2005 በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ በተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርት ከ5 ሺህ በላይ ጎልማሶች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ መሆኑን የወረዳው ትምህርት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ አዝመራ አመኑ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በወረዳው በሚገኙ ከ35 በሚበልጡ ትምህርት ቤቶችና ጊዜያዊ የማሰተማሪያ ስፍራዎች ማንበብና መጻፍ ለማይችሉ ጎልማሶች ትምህርት እየተሰጠ ነው። በወረዳው ማንበብና መጻፍ የማይችሉ ጎልማሶችን በመለየትና ለ96 አመቻቾች የማስተማር ስነዘዴ ስልጠና በመስጠት 5 ሺህ 947 ጎልማሶች ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። በደረጃ አንድና ሁለት ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ካሉት ጎልማሶች በተጨማሪ በቀበሌ አመራሮች በልማት ቡድኖችና በአንድ ለአምስት ትስስር አማካኝነት ማንበብና መጻፍ የማይችሉ ጎልማሶች እየተለዩ መሆኑንና በአሁኑ ወቅት በወረዳው የጎልማሶች ትምህርት ሽፋን ከ56 በመቶ በላይ እንደደረሰ አቶ አዝመራ ተናግረዋል። የጎልማሶች ትምህርትን በተጠናከረ መልኩ ለማከናወን የወረዳው አስተዳደር ለአመቻቾች አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝና የማስተማሪያ መጽሀፍት ግዥ በመፈጸም ለሁሉም ጣቢያዎች እንዲዳረስ ማድረጉን አስታውቀዋል። በተጨማሪም አምስትና ስድስት ዓመት የሆናቸው 23 ሺህ 233 ህጻናት በ250 አመቻቾች የቅድመ መደበኛ ትምህርት በትምህርት ቤትና ከትምህርት ቤት ውጪ በተዘጋጁ የማስተማሪያ ስፍራዎች እየተማሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ልዩ ፍላጎት ያላቸውን አካል ጉዳተኞች በአካቶ የማስተማር ዘዴ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ 392 መስማትና ማየት የተሳናቸውና የተለያየ የአካል ጉዳት ያለባቸው ህጻናት በሰለጠኑ መምህራን እንዲማሩ መደረጉን አቶ አዝመራ ጠቁመዋል። የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ

የሀዋሳ ዩኒቨርሰቲ የህብረተሰብ አገልግሎትን ለማጠናከር እየሰራ ነው ይላል

Image
አዋሳ ግንቦት 22/2005 የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የህብረተሰብ አገልግሎትን እንደ መደበኛ ፕሮግራሙ በማቀፍ የምርምር ውጤቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ስራውን አሰፋፍቶና አጠናክሮ መቀጠሉን የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ገለጹ፡፡ ዩኒቨርስቲው ለስራ አጥ ወጣቶችና ሴቶች በዘመናዊ የዶሮ እርባታ ዙሪያ ያዘጋጀው ስልጠና ትናንት በሀዋሳ ከተማ ተጀምሯል፡፡ ስልጠናውን የከፈቱት የዩኒቨርሰቲው ፕሬዚደንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ እንደገለጹት የመማር ማስተማር ስራቸውን ከምርምር ጋር አቀናጅተው ያገኟቸውን አዳዲስና ችግር ፈቺ ውጤቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ስድስት የቴክኖሎጂ መንደሮች ተቋቁመዋል፡፡ የህብረተሰብ አገልግሎትን እንደ መደበኛ ፕሮግራማቸው በማቀፍ በምርምር የተገኙ የግብርና፣ የጤናና ሌሎችን ውጤቶችን በተለይ ስራ አጥ ወጣቶችንና ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተለያዩ ስልጠናዎችንና የመስሪያ ግብአቶችን በማሟላት ድጋፍ እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ ብቻ በደን ልማትና ችግኝ እንዲሁም በእንጉዳይ አመራረትና አጠቃቀም ላይ ከሀዋሳ ከተማና ከሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ ለተወጣጡ በርካታ ወጣቶችና ሴቶችን ተጠቃሚ ማድረጋቸውን አመልክተው አሁንም ለ24 ወጣቶች በዘመናዊ የዶሮ እርባታ ዙሪያ ስልጠና አዘጋጅተው እራሳቸውን ችለው በተመሳሳይ ለሌሎችም የሚበቁበት የአቅም ግንባታ ድጋፍ አያደረጉ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ስራ ፈጣሪ ወጣቶችን እናበረታታለን ያሉት ዶክተር ዮሴፍ ዩኒቨርስቲው አጠቃላይ የትምህርት ተቋም እንደመሆኑ ሌሎችንም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የምርምር ውጤቶችን ለህብረተሰቡ በማሸጋገር ተጠቃሚ ለማድረግ ስራቸውን በሁለገብነት አስፋፍተውና አጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል፡፡ በዩኒቨርስቲው የምርምርና ልማት ዳይሬክተር ዶክተር ተስፋዬ አበበ በበኩላቸው ህብረተሰቡ ተጠ

Cooking with traditional crops improves nutrition and boosts women's incomes

Image
Promising pulses in Ethiopia A similar healthy-eating effort is underway in Ethiopia, where about 52% of the country's rural population fails to meet minimum consumption requirements for calories. Researchers at the University of Saskatchewan and Hawassa University are studying how education can increase consumption of pulses, including chickpeas, broad beans, and lentils. They are focusing particularly on the consumption patterns of the most vulnerable: children under five, adolescent girls, and adult females. Studies found a lack of awareness among women of the nutritional value of pulses, and the need to incorporate this high-protein, high-iron crop in everyday meals. "The main staple of the Ethiopian diet is teff (a local cereal grain). People would rather eat that alone than add a little protein, like lentils. Part of our project is showing them the nutritional value of protein combinations. We are also trying to overcome the perception of pulse as 'poor man'