Posts

በደኢህዴን መሪነት የክልሉ ህዝቦች አንድነት ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት ጎልብቷል

Image
አዋሳ፤ መጋቢት 10/2005/ዋኢማ/ - በደኢህዴን መሪነት የደቡብ ክልል ሕዝቦች በፈቃዳቸው የመሰረቱት ክልላዊ መስተጋብርና አንድነት በሀገሪቱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት መስክ ዲሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት እንዲጎለብት ጠንካራ መሰረት መጣሉን የደኢህዴንና ኢህአዴግ ሊቀመንበር ገለጹ። የደኢህዴንና ኢህአዴግ ሊቀመንበር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የደኢህዴን 8ኛ ጉባኤ ትናንት በሀዋሳ ከተማ ሲጀመር እንደገለጹት፤ በክልሉ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መካከል የነበረው መስተጋብር በጋራ መልማትና አስተማማኝ ሰላም የማረጋገጥ ፍላጎት በመሆኑ ጠንካራ ክልል እንዲመሰርቱ አስችሏል። ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ባሏቸው የታሪክ የስነ-ልቦናና የተለያዩ መስተጋብሮቻቸው በአንድነት በመሰረቱት ክልል በደኢህዴን አመራር ልዩነታችን ውበታችን አንድነታችን ጥንካሬያችን ሆኖ በተሃድሶ መስመር ላገኘነው ድልና ለተመዘገበው ፈጣን ልማት መሰረት መሆኑን ተናግረዋል። እስከ ደኢህዴን ሰባተኛ ጉባኤ በክልሉ ለሰባት ተከታታይ ዓመታት የባለ ሁለት አሃዝ የኢኮኖሚ ዕድገት መመዝገቡ 7ኛው የድርጅቱ ጉባኤ ተከታታይ ፈጣን ዕድገት ማስመዝገብ ብቻውን በቂ ባለመሆኑ ይህንን ዕድገት በማስቀጠል የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ማምጣት እንዳለበት ወስኖ ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል። ደኢህዴን የተከተለው መስመር ተከታታይና ፈጣን ልማትን ከማረጋገጥ ባሻገር የክልሉ ህዝቦች ከልማቱ በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበትና ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል የሚያረጋግጥ መሆኑን በተግባር እንዳስመሰከረ አቶ ኃይለማሪያም አስታውቀዋል። ደኢህዴን የክልሉን ህዝቦች ከዳር እስከዳር የማንቀሳቀስ ብቃቱን በመጠቀም ልማትን ብቻ ሳይሆን ዴሞክራሲ በህዝቡ ቀጥተኛ ተሳትፎ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ማድረጉን አስረድተዋል። ንቅናቄው በ

የአለታ ወንዶ ወረዳ ሴቶች ለምርጫው መዘጋጀታቸውን ገለጹ

አዋሳ መጋቢት 09/2005 በመጪው ሚያዚያ ወር በሚካሄደው የዞን፣ የወረዳና ቀበሌ ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ መጋጀታቸውን በሲዳማ ዞን የአለታ ወንዶ ወረዳ ሴቶች ገለጹ፡፡ ከወረዳው ሴቶች መካከል አንዳንዶቹ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በምርጫው መብትና ጥቅማቸውን የሚያስከብርላቸውን ለመምረጥ ከወዲሁ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የወረዳው ሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጽሕፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ አዛለች ካያሞ እንዳስረዱት በአለታ ወንዶ 29 የገጠርና ከተማ ቀበሌዎች ለምርጫው ከተመዘገበው 59ሺህ ያህል ህዝብ ግማሽ ሴቶች ናቸው፡፡ በተመራጭ፣በአስመራጭና ታዛቢነት ከወንዶች እኩል ስብጥርና ተሳትፎ እንዳላቸው አስታውቀው በመራጭነትና በተመራጭነት የተመዘገቡት ሴቶች በስርዓቱ ያገኙትን ተጠቃሚነት ዘላቂ ለማድረግ ሰርተው የሚሰሩ ተወካዮቻቸውን ለመምረጥ እለቱን በጉጉት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ በድርጅት ለወረዳ ምክር ቤት በዕጩነት ከቀረቡት መካከል ወይዘሮ አልማዝ ዲንጋሞ ቢመረጡ ሴቶች ከወንዶች እኩል ሆነው በማህበራዊ ፣ በኢኮኖሚና ፓለቲካ ያላቸውን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ጠንክረው ለመስራት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ በድርጅታቸው ተወክለው ለምርጫው ተሳታፊ በመሆናቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ በመራጭነት ከተመዘገቡት መካከል ወጣት አሰለፈች በቀለና እመቤት ተሰማ ሴቶች ለዘመናት ሲደረስባቸው ከነበረው የጾታ ተጽዕኖናና ጭቆና ተላቀው ባገኙት መብት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀው በቀጣዩ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ጥቅሞቻቸውን የሚስጠብቁላቸውን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል፡፡

ደኢህዴን ያስገነባው አዳራሽና ማሰልጠኛ ማዕከል ተመረቀ

አዋሳ መጋቢት 09/2005 የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢህዴን/ ከ64 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ በጀት ያስገነባው ቢሮ ማስልጠኛ ማዕከልና የመሰብሰቢያ አዳራሽ ዛሬ ተመረቀ። ድርጅቱ ከአባላት መዋጮ ባሰባሰበው ገቢ የክልሉን ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ባህላዊና ፖለቲካዊ እሴቶችን በሚያንጸባርቅ ሁኔታ ያስገነባውን ቢሮ ማሰልጠኛ ማዕከልና የመሰበሰቢያ አዳራሽ መርቀው የከፈቱት የደኢህዴንና ኢህአዴግ ሊቀመንበር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ናቸው። በ548 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የተገነባውና ለቢሮ አገልግሎት የሚውለው ባለሁለት ፎቅ ህንጻ 57 ለተለያየ አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎችና አራት የመሰብሰቢያ አዳራሾችን የያዘ ነው። የጉባኤ አዳራሹ በአንድ ሺህ 790 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈና በአንድ ጊዜ አንድ ሺህ 360 ሰዎችን የመያዝ አቅም ያለው ቁሳቁስ የተሟሉለትና ሶስት መለስተኛ የመወያያ ክፍሎች ፣የእንግዳ ማረፊያዎች ያሉት መሆኑ ተገልጿል። በአንድ ጊዜ ሁለት ሺህ 500 ሰልጣኞችን ተቀብሎ ማስተናገድ የሚችለው የስልጠና ማዕከል 30 የስልጠና ክፍሎች ፣10 የአስተዳደር ቢሮዎችና ሌሎች አገልግሎት መስጫ ክፍሎችን የያዘ በአንድ ሺህ 760 ካሬ ሜትር ቦታላይ ያረፈ መሆኑ ተገልጿል። http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=6432&K=1

Ethiopia’s Human Rights Crisis Worsened

By Betre Yacob. The human rights situation in Ethiopia, the most important strategic and security ally of the Western powers, has worsened drastically, according to the 2013 Human Rights Watch’s World Report, which summarizes the human rights situation of more than 90 countries worldwide—drawing on events from the end of 2011 through November 2012. The 665 page report says that Ethiopia’s dictatorial regime has deliberately continued to severely restrict fundamental rights of freedom of expression, association, and assembly. In addition, the report indicates that intimidation, arbitrary arrest, torture, forced displacement, and killing remain routine throughout the country. The report, which reflects extensive investigative work that Human Rights Watch undertook in collaboration with local human rights activists, was released in the beginning of February 2013. Providing heartbreaking examples, cases, and photographs, the report explains enough how dramatically the human rights

የደ.ኢ.ህ.ዴ.ን. 8ኛ ጉባዔ በሀዋሳ ተጀመረ

Image
የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደ.ኢ.ህ.ዴ.ን./ 8ኛ ጉባዔ መጋቢት 9/2005 ረፋድ ላይ በሀዋሳ ከተማ ተጀመረ፡፡ በጉባዔው መክፈቻ የድርጅቱ ሊቀመንበር ጠቅላይ ሚ/ር ኃይለማርያመ ደሳለኝ  ደ.ኢ.ህ.ዴ.ን. መስመሩን በማጥራትና ልማታዊ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብን በማጉላት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርግ ልማት እንድረጋገጥ አድርጓል ብለዋል፡፡ በደቡብ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ለተመዘገበው የኢኮኖሚ እድገት የክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ሚና እንደነበረው አቶ ኃይለማርያም ገልፀዋል፡፡ የታላቁ መሪ መለስ ዜናዊን መስዋዕትነት ተከትሎ የክልሉ ህዝብ ራዕያቸውን ለማስቀጠል በገባው ቃል መሰረት የህዳሴ ጉዞውን ለማሳካት እየተካሄደ ያለው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል፡፡ በደቡብ ክልል የተጀመሩትን የልማት ስራዎች በማጠናከርና ለልማት ሰራዊት ግንባታ ትኩረት በመስጠት በተደራጀ መልኩ ሁለንተናዊ ዕድገት ለማስመዝገብ የድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች የአመራርነት ሚናቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና የድርጅቱ ም/ሊቀመንበር አቶ ሽፈራው  ሽጉጤ  በበኩላቸው የታላቁ መሪ መለስ ዜናዊ ሁለንተናዊ የልማት ስራዎችን በእልህ ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ጥረት በሚደረግበት ወቅት ላይ ጉባዔው የሚካሄድ መሆኑን በመግልጽ በሰላም በድልና በልማት ጎዳና ሆነን  የሚካሄደውን ጉባዔ ውሳኔዎች የክልሉ ህዝብና መንግስት ለማስፈፀም ዝግጁ ናቸው ብለዋል ፡ ፡ በጉባዔው ላይ 1200 ታዳሚዎች  በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ የተለያዩ ፓርቲዎች ለደ.ኢ.ህ.ዴ.ን. ያላቸውን አጋርነት በመግለፅ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ http://www.ertagov.com/amerta/component/content/article/48-erta-tv-today-top-