Posts

የግብርና ሚኒስቴር የገጠር መሬት የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በድጋሚ ሊሰጥ ነው

ግብርና ሚኒስቴር ለሁለተኛ ጊዜ በአራት ክልሎች ውስጥ ለሚገኙ 50 ሚሊዮን ማሳዎች በካዳስተር ካርታ የተደገፈ የገጠር መሬት ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ሊሰጥ ነው፡፡ የካዳስተር ካርታ ሥራውን የሚያካሂዱት የኢትዮጵያ ካርታ ሥራ ኤጀንሲና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ናቸው፡፡ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ጌታሁን፣ የኢትዮጵያ ካርታ ሥራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሡልጣን መሐመድና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጄነራል ተክለብርሃን ወልደአረጋይ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡ ነገር ግን የግብርና ሚኒስቴር ለዚህ ፕሮጀክት የሚያስፈልገውን ፋይናንስ በእጁ ባለማስገባቱ ሥራው እንዳልተጀመረ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ግብርና ሚኒስቴር የሚያስፈልገውን ገንዘብ የዓለም ባንክ እንዲያቀርብለት ጥያቄ አቅርቧል፡፡ የዓለም ባንክ ገንዘቡን በቅርቡ እንደሚለቅ ምንጮችም ገልጸዋል፡፡ ገንዘቡ እንደተለቀቀ ደኅንነት ኤጀንሲ ማሳዎቹን የአየር ፎቶ ያነሳል፡፡ ያነሳውንም ፎቶ ለካርታ ሥራ ኤጀንሲ ያስረክባል፡፡ ካርታ ሥራ ኤጀንሲ የማሳዎቹን ካርታ እንደሚሠራና ለሚኒስቴሩ እንደሚያስረክብ ታውቋል፡፡ ቀደም ባሉት ዓመታት መንግሥት በየክልሉ በባህላዊ የአሠራር ዘዴ በመጀመርያ ደረጃ የገጠር መሬት የይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት በማዘጋጀት 90 በመቶ ለሚሆኑ አርሶ አደሮች ማደሉ ታውቋል፡፡ ነገር ግን ቀደም ሲል የቀረበው ካርታ የተጠናከረ መረጃ የማይሰጥ በመሆኑና በመጀመርያ ደረጃ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ላይ የነበሩበትን ክፍተቶች በማስተካከል እንደ አዲስ መረጃ የሚሰጥ ካርታ መስጠት እንደሚገባ ታምኖበታል፡፡ የገጠር መሬት አስተዳደር ሥርዓቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ የካዳስተር የመሬት መረጃ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ ተኝቷል ተብሏል፡፡ አዲ

ለከተማ ኣስተዳደር ምክር ቤት ለሚካሄደው ምርጫ ሲኣን150 እጩዎችን ኣስመዘጋበ

Image
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 8 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ሚያዝያ ወር ለሚካሄደው ምርጫ የሚወዳደሩትን እጩዎች ይፋ አደረገ። ዛሬ ማምሻውን ከብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባገኘነው ጊዜያዊ መረጃ መሰረት  ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ለመወዳደር 11 ፓርቲዎች እጩዎቻቸውን አስመዝግበዋል። በዚህም መሰረት ኢህአዴግ 138 ፣ ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ  87፣ የመላው ኢትዮጵያውያን ብሄራዊ ንቅናቄ መኢብን 85 እንዲሁም የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ ኢራፓም 14 እጩዎችን አስመዝግበዋል። የመላው ኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መኦህዴፓ 14፣ የኢትዮጵያ የፍትህና የዶሞክረሲ ኃይሎች ግንባር ኢፍዴሃግ 9 ፣ የኢትዮጵያ ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ኢሰዴፓ 6፣ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ንቅናቄ ኢዴአን 3፣ የገዳ ስርዓት አራማጅ ፓርቲ ገስአፓ 2 ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ኢዴፓ 1 እጩዎችን ሲያመዘግቡ በድምሩም ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 393 እጩዎች ተመዝግበዋል። አዲስ አበባ ላይ ለክፍለ ከተማ ምክር ቤት ኢህአዴግ 3ሺ 480 እጩዎቹን ሲያስመዘግብ ለወረዳ ምክር ቤትም እንዲሁ 34ሺ 794 እጩዎችን ነው ያስመዘገበው። ኦሮሚያ ክልል ላይም ለከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ምርጫ ኢህአዴግ ፥ 2 ሺህ 205 እጩዎችን ሲያስመዘግብ ፤ መኦህዴፓ 5፣ እንዲሁም ገስአፓ 1 እንዲሁም አምስት የግል ተወዳዳሪዎችም እጩዎቻቸውን አስመዝግበዋል። ደቡብ ከልል ላይ ለከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ለሚካሄደው ምርጫ ኢህአዴግ 1ሺህ 160 ፣ የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ሲአን 150 ፣ ኢዴፓ፣ ኢፍዲሃግና ኢራፓም በድምሩ 12 እጩዎችን  ፣ የወላይታ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ዎህዴግ 1 እንዲሁም ሁለት እጩዎችም በግ

የእለቱ የሲዳማ ዜና በደቡብ ቲቪ 2/14/2013

Image
የእለቱ የሲዳማ ዜና 2/14/2013 የእለቱ የሲዳማ ዜና በደቡብ ቲቪ

በደቡብ ክልል ስድስተኛው የአርሶ አደሮች ቀን በመጪው ሳምንት መጨረሻ ላይ በሀዋሳ ይከበራል

አዋሳ የካቲት 07/2005 ስድስተኛው የአርሶ አደሮችና ከፊል አርሶ አደሮች በዓል በደቡብ ሕዝቦች መስተዳድር በክልል ደረጃ ከየካቲት 16 ቀን እስከ 18/2005 እንደሚከበር የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ። በበዓሉ ላይ በግብርናው ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ አርሶ አደሮችና ባለድርሻ አካላት ይሸለማሉ። በቢሮው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሂደት ተወካይ አቶ ሊሬ አቢዩ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ለስድስተኛ ጊዜ በክልሉ በሚከበረው በዓል ላይ 660 አርሶ አደሮች ከፊል አርሶ አደሮች የልማት ባለሙያዎች በግብርናው ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይሸለማሉ። ''የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የመለስን የብልፅግና ራዕይ እናሳካለን'' በሚል መሪቃል በሚከበረው የክልሉ አርሶ አደሮች በዓል ተሸላሚ ከሚሆኑ 660 ባለድርሻ አካላት 390ዎቹ አርሶ አደሮች መሆናቸውን ገልፀዋል። ከተሸላሚ አርሶ አደሮች መካከል 117 ከግብርና ተነስተው እሴት በመፍጠር ወደ ባለሀብትነት ደረጃ በማደግ በሌላ መስክ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙባቸው መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም 82 ሴት አርሶ አደሮችና 54 ወጣት አርሶ አደሮች እንዲሁም የእረፍት ጊዜያቸውን ከአርሶ አደሩ ጋር በማሳለፍ በግብርናው መስክ ለተገኘው ውጤት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ 167 የልማት ባለሙያዎች እንደሚገኙበት አስታውቀዋል። በክልል ደረጃ ተሸላሚ ከሚሆኑት መካከል 171 አርሶ አደሮችና ባለሙያዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚከናወነው የአርሶ አደሮች ቀን ላይ ተሸላሚ እንደሚሆኑ አቶ ሊሬ ጠቁመዋል። http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=5486&K=1

የኢህኣዴግ_ ደኢህዴን ኣባል እና በተወካዮች ምክር ቤት የሲዳማ ህዝብ ተወካይ ብሎም የህዝብ ተመራጭ የነበሩት የተከበሩ ወይዘሮ ከበቡሽ ካዊሶ ገዥውን ፓርቲ በመክዳት በኣሜሪካ የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቀዋል ተባለ

የኢህኣዴግ_ ደኢህዴን ኣባል ፤ በተወካዮች ምክር ቤት የሲዳማ ህዝብ ተወካይ እና የህዝብ ተመራጭ የነበሩት የተከበሩ ወይዘሮ ከበቡሽ ካዊሶ ገዥውን ፓርቲ በመክዳት በኣሜሪካ የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቀዋል ተባለ ከሲዳማ ኣርነት ግንባር ድህረገጽ ላይ የተገኘው መረጃ  እንደምያሳየው ፤ የተከበሩት ወይዘሮ  ከበቡሽ ለምን ገዥውን ፓርቲ  እንደከዱ እና በምን መንገድ ወደ ኣሜሪካን ልገቡ እንደቻሉ የታወቀ ነገር የለም። ተጨማሪ ዘጋባ ከታች ያንቡ፦ Member of Ethiopian Parliament Defects to US February 10, 2013-A member of Ethiopia ruling party, Mrs. Kebebush Kawisso, has defected to US and is currently seeking political asylum, according to our sources. She was the representative of Sidama people’s democratic organization (SPDO), an organization that EPRDF created and uses to suppress the democratic aspirations of Sidama people. Sources disclosed that, ongoing atrocities against Sidama people led to her decision to defect in protest. Her defection comes in the midst of ever increasing miseries launched against Sidama people by Tigeans controlled Ethiopian government. It's recalled that Sidamas who have spoken up against injustice have been