በሀዋሳ ከተማ የተጀመረው የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ባለስድስት ፎቅ ህንጻ ግንባታ በመገባደድ ላይ ነው
አዋሳ ጥር /2005 የኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም በደቡብ ክልል ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን የብድርና የቁጠባ አገልገሎት ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ ። ተቋሙ በክልሉ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያስጀመረው የኦውቶሞቲቭ ፕሮጀክት ግንባታ በመፋጠን ላይ መሆኑም ተገልጧል ። የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙሰማ ጫሊ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ባለፈው አመት በተጀመረው የፕሮጀክት ሀዋሳ ከተማ የሚገኘው የተቋሙን ዋና መስሪያ ቤት በዞን፣ በልዩ ወረዳና በወረዳ ደረጃ ካሉት 172 ቅርንጫፎች ጋር በኮምፒተር ኔት ወርክ የማያያዝ ስራ እየተካሄደ ነው፡፡ በተጨማሪ በሀዋሳ ከተማ የተጀመረው የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ባለስድስት ፎቅ ህንጻ ግንባታ በመገባደድ ላይ እንደሚገኝና በሚቀጥለው ወር ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ አስረድተዋል፡፡ በክልሉ የ12 ቅርንጫፎች ባለሁለት ፎቅ ህንጻ ግንባታ በቅርቡ መጀመሩንና በ119 ንዑስ ቅርንጫፎች ከተጀመረው የቢሮ ግንባታ ውስጥም እስካሁን የ40ዎቹ ስራ ሲጠናቀቅ የቀሪዎቹ እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ይከናወናል ብለዋል ። በየደረጃው ያሉት ሁሉም ቅርንጫፎ ቢሮዎችን በማሻሻል በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ የታገዘ የኮምፒተር ኔት